Tuesday, 8 April 2014

በዓረና ከፍተኛ አመራሮቸ፣አባሎችና ዓረና በጠራው ህዝባዊ ስብሰባ ተሳታፊዎች የተፈፀመው ኢ ሰብአዊ እንግልት – ብርሃኑ በርሄ (የዓረና ፕሬዘዳንት)

April 7th, 2014
ዛሬ እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ/ም ዓረና ትገራይ ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ በምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወንበርታ ወረዳ ጠርቶ ያካሄደ ሲሆን ከትናትና ጀምሮ ህዝቡን ወደ ስብሰባው እንዲመጣ የሚቀሰቅሱ አባሎችና አመራሮች ከድንጋይ ውርወራና የቡድን ረብሻ ባለፈ ከተከራዩት አልጋ አስወጥቶ ሌሌት የትም ተጥለው እንዲወድቁ ለማድረግ እጅግ ኢ-ሰብአዊ ተግባር መፈፀሙን ተገልፆ ነበር ፡፡ የአፅቢ ፖሊስ አባላቶቻችን ከተከራየትና ገንዘቡን ከፍለው የክፍሉ ቁልፍ ተረክበው በእጃቸው ከሚገኝ ቤት ካለወጣሁ በማለት ትናንት መጋቢት 27 ቀን 2006 ዓ/ም አቶ አምዶም ገ/ሰላሴ ፣ አቶ ስልጣኑ ሕሸ ፣ መም/የማነ ንጉሰ እስከምሽቱ 2፡30 በአፅቢ ፖሊስ በእስር ነበሩ ፡፡ በዚሁ ቀን የወረዳ አስተዳዳዎች የሚመሩት ለህዝብ የሚታደል በራሪ ፅሑፍ መቅደድና በአራና አባላት ላይ ድንጋይ በመወርበር ሲያውኩ ዛሬ ጥዋት ደግሞ ቦዘኔ ህፃናትና ምልምል ካድሬዎች ገብረ ማርያም የተባለው የታጠቁ ምልሻ ጭምር በዓራና አባላት ላይ መጠነ ሰፊ የማወክ ተግባር እንደጀመሩና ስብሰባው እንዳይካሄድ ከፍተኛ ጥረት እንዳደረጉ ተገልፆ ነበር ፡፡
ዛሬ ከሰኣት በሁዋላ የህዝብ ስብሰባው እንደተጠናቀቀ ደገሞ የአረና ከፍተኛ አመራሮችና አባሎች እንዲሁም በስብሰባው የተገኙ ወደ 61 የሚሆኑ ገበሬወች በአፅቢ ከተማ ፖሊስ ጣብያ ታስረዋል ፡፡ የእስሩ መነሻ ምክንያት ተደባዳቢ የወንጀለኞች ቡድን የአረና አባላትን ሲደበድቡና ስብሳባው እንዳይጀመር ሲያውኩ የሚያሳይ መረጃ በሞባይል ቀርፃችሁዋል የሚል ሆኖ ተቀረፀ የተባለው ፊልም ከተገኘበት የሞባይል ስልክ አውጥቶ ለመንጠቅና ለማጥፋት ያለመ ነው፡፡
የአቶ አብርሃ ደስታ ሞባይል ተወስዶ እየተፈተሸ ሲሆን የሌሎቹ የአረና ከፍተኛ የአመራር አባላትና አባላት ሞባይል ስልኮችም እንዲሁም በስብሰባው የነበሩ ገበሬዎች ሞባይል በፖሊስ ተነጥቆ በአፅቢ ፖሊስ ጣብያ እስር ቤት እየተፈተሸ እንደሆነ ቦታው ያሉ የአረና አባላት ሪፖርት አድርገውልኛል ፡፡
ሁኔታው ለትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘአማኑኤል ለገሠ በሞባይል ስልካቸው 0914 300868 ልክ ዛሬ እሁድ ከሰአቱ 9፡30 ደውየላቸው ስልኩን እንዳነሱ የምደውልላቸው ያለሁኝ ብርሃኑ በርሀ መሆኔን ገልጨ ልክ በኩሓ አፀያፊ እስርና መንግላታት በዓረና አባለት እየተፈፀመ እንዳለ ሪፖርት ሳደርግላቸው እኔን መሆኔን እንዳወቁ ወዲያው ስልካቸውን የዘጉብኝ እንዳይሆን ብየ ስልኩን እንዳይዘጉብይ በፍጥነት በአፅቢ ስብሰባ የሚያካሂዱ አባላቶቻችን መታሰራቸው ስነግራቸው ንግግሬን ሳልጨርስ ስልኩን ዘጉት ፡፡
ፖሊስ ወንጀል ስለመሰራቱ ማስረጃ የያዘለት ይሸልማል እንጂ ወንጀል መሰራቱን የሚያረጋግጥ መረጃ ለማጥፋት ፖሊስ የሚሰራ ከሆነ ይህ ዓይነቱ ፖሊስ የሰላም አባት ወይስ የወንጀል አባት እንበለው ?
አሁን በፖሊስ ምርመራ በአፅቢ ፖሊስ ጣብያ የሚገኙት 1- አቶ ስልጣኑ ሕሸ የዓረና የድርጅት ጉዳይ ሃላፊና የፅሕፈት ቤት ሃላፊ 2- አቶ ዓምዶም ገብረ ስላሴ የዓረና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ 3- አቶ አብርሃ ደሰታ የዓረና የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ አባልና ስራ አስፈፃሚ አባል 4- መም/ ታደሰ ቢተውልኝ የዓረና ማእከላዊ ኮሚቴ አባል 5- አቶ አስገደ ገብረ ስላሴ 6 – መም/የማነ ንጉሴ 7 አቶ ሃይለ ኪሮስ ታፈረ 8- መም/ ሃይለ 9 አቶ ቴወድሮስ 10 – መምህር ክፍሎም እና ሌሎች የአረና አባላትና 61 የስብሰባው ተሳታፊ የአከባቢው ገበሬዎች ናቸው፡፡
ዓረና ትገራይ ፓርቲ ይህንኑ ዘግናኝ የገዢው ፓርቲ የዓፈና ተግባር እንዲቃወምና እንዲያጋልጥ ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ፣ ለሰብአዊ መብት መከበር የሚሰሩ ተnማት ፣ በኢትዮጵያ ለሚሰሩ የውጭ መንግስታት ኢንባሲዎች እንዲሁም ድምፃቸው ለታፈኑ ድምፅ ለመሆን ለሚሰሩ የሃገር ውስጥና የውጭ ሚድያዎች ጥሪውን ያቀርባል ፡፡ በተጨማሪም እነዚህ የጠራራ ፀሃይ ወንጀለኛች በሕግ ፊት ለመፋለም ይረዳ ዘንድ የቻለ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ለዓረና ትገራይ ፓርቲ የገንዘብና የሙ ድጋፍ እንዲያደርጉ ለሁሉም ወንጀል የሚፀየፉ ወገኖች ጥሪውን ያቀርባል ፡፡
ይህ ዓይነቱ ዓይን ያወጣ ወንጀል የትግራይ ህዝብ ከደርግ አፈና ለመታደግ በ 17 የትጥቅ ትግል ዓመታት ሂወታቸውና ንብረታቸው ለከፈሉ በሂወት ያሉ ለውጥ ፈላጊዎቹ የህወሓት አባለትና ደጋፊዎች እንዲሁም መላ የትግራይ ህዝብ በአማራጭ ሰላማዊ ትግል ለሚያካሂድ ፓርቲ የሚፈፀም ጭፍጨፋ በእራሱ መብት የተቃጣ ወንጀል መሆኑን አውቆ ብምሬት እንዲቃወመው ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ጭፍን ዓፈና የነፃት ባለ ራአዮችን በማጠናከር የነፃነት ራእይ ገዳዮችን የሚያዳክም ግብዝ ውሳኔ መሆኑን የትግራይ ህዝብ አኩሪ ፀረ ባእዳዊ ገዥዎችና ፀረ ፋሽት ደርግ ተጋድሎ በሚገባ ያስተማረን በመሆኑ በዚሁ እኩይ የደርግን አሻራ የወረሱ የአምባገነኖች ተግባር ዓረና ፓርቲና አባላቱ እንደማይንበረከኩ ሁሉም ሊያቀው ይገባል ፡፡ የዓረና ሃገራዊ ራኢ የሃገር አጀንዳ ሆኖ በሃረዊ ለውጥ ይደምቅ ዘንድ ዓረና ጠንክሮ እንደሚሰራም ደግሞ ያረጋግጣል ፡፡
ዓረና ትገራይ ፓለዴሞክራሲና ለሉእላዊነት ፓርቲ
መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ/ም ከቀኑ 10፡20

No comments:

Post a Comment