Tuesday, 29 April 2014

ፖሊስ የጣይቱ ልጆችን ለማሸማቀቅ እየጣረ ነው

April 29, 2014
ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ለተደረገው ሰልፍ ቅስቀሳ ላይ እያሉ ፖሊስ ‹‹የእውቅና ደብዳቤው አልደረሰኝም፣ ህገ ወጦች ናችሁ!›› ብሎ ያሰራቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት (የጣይቱ ልጆች) ላይ ፖሊስ የተለያዩ የማሸማቀቂያ ስልቶችን እየወሰደ ይገኛል፡፡ በዛሬው ቀን ፖሊስ ታሳዎቹን በተለይም ሜሮን አለማየሁና ንግስት ወንዲፍራውን ‹‹እስር ቤቱን በመረበሽ›› በሚል ሌላ ክስ ከግቢ አስወጥተው ቃል ተቀብለዋቸዋል፡፡ በወቅቱም ማስፈራራትና ዛቻ እንደደረሰባቸው ታሳሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
የጣይቱ ልጆች በታላቁ ሩጫ ላይ በፖሊስ በተያዙበት ወቅት ፖሊስ የተለያዩ በደሎችን ለመፈጸም ሲጥር መብታቸውን ለማስከበር ባደረጉት ጥረት ፖሊሶች ሌሊት ከግቢ አስወጥተው የድብደባና ሌሎች ማስፈራሪዎችን እንዳደረጉባቸው ይታወሳል፡፡
በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ እስር ቤቶች የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ምግብ እንዳይገባላቸው፣ ቤተሰብ እዳይጠይቃቸውና ሌሎችንም መብታቸውን የሚጋፉ በደሎች እየተፈጸሙባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያYoung semayawi party female activists

የእሪታ ቀን ለሚያዚያ 26 በአስተዳደሩ እውቅና አገኘ – ሰነድ ይዘናል

April 29th, 2014
የአንድነት ፓርቲ የፊታችን ሚያዚያ 26 ቀን በአዲስ አበባ ሰልፍ እንደሚያደርግ ማሳወቁ ይታወቃል። መጋቢት 28፣ ሚያዚያ 5፣ ሚያዚያ 19 ሰልፍ ለማድረግ ጠይቆ ፣ አስተዳደሩ በተለያዩ ምክንያቶች እውቅና ለመስጠት ፍቃደኛ ባለመሆኑ ነበር አንድነት የሰልፉን ቀን ለሚያዚያ 26 ያስተላለፈው።udj_permit

አንድነት ፓርቲ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለሆኑት Jhon Kerry በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ጉዳይ ደብዳቤ ፃፈ፡፡

April 29th, 2014                 
አንድነት ፓርቲ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለሆኑት Jhon Kerry በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ጉዳይ ደብዳቤ ፃፈ፡፡10320615_627627183988886_4211223085947002378_n

ESAT Eneweyaya April 29, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Eneweyaya April 29, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Eneweyaya April 29, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Eneweyaya April 29, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Eneweyaya April 29, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Eneweyaya April 29, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Eneweyaya April 29, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Eneweyaya April 29, 2014 Ethiopia | ESAT Tube

Monday, 28 April 2014

የጋዜጠኞቹና የአክቲቪስቶቹ እስር አሳሳቢ ነው፡፡ – ከኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ(ኢጋመ) የተሰጠ መግለጫ

April 28th, 2014  
ትላንት ሚያዝያ 17 2006 አመሻሽ ላይ ዞን 9 በተሰኘ ድረ ገጽ (ብሎግ) ላይ በሳል ፖለቲካዊና ማህበራዊ ትችቶችን በማቅረብ ከሚታወቁት ፀኀፍት መሀከል 6ቱ ማለትም ማህሌት ፋንታሁን፣ በፍቃዱ ሀይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ዘላለም ክብረት፣ አጥናፍ ብርሀን፣ አቤል ዋበላ እንዲሁም ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣ ጋዜጠኛ አስማመው ኃ/ጊዎርጊስ እና ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል፡፡
ግለሰቦቹ በተለያየ ቦታ በየስራ ገበታቸው ላይ እያሉ ሁሉም በተመሳሳይ ሰዓት በፀጥታ ሀይሎች ተይዘው በማዕከላዊ ምርመራ ማዕከል ታስረው የሚገኙ ሲሆን፤ የተለያዩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት እስሩ በደንብ የታሰበበት ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ታሳሪዎቹ ታሰሩ ከተባለበት ሰዓትና ደቂቃ ጀምሮ የሚገኙበትን አጠቃላይ ሁኔታ ለማጣራት አየሰራ ሲሆን ፤ እስካሁን በሰበሰበው መረጃ መሰረት ልጆቹን ለእስር የሚያበቃ ምን አይነት ማስረጃ እንደተገኘባቸው ለማወቅ አልቻለም፡፡
ሆኖም ግን ለእስር ከመዳረጋቸው በፊት ከመንግስት ሲርስባቸው በነበረው ህገወጥ ድርጊቶች ምክንያት ለረጅም ጊዜ ስራቸዉን ካቋረጡ በኋላ በቅርቡ ወደ ስራ መመለሳቸዉን ይፋ አድርገው እንደ ነበር ከድረ-ገጻቸው ላይ ለመረዳት ችለናል፡፡ ይህ ጉዳይ እስሩን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎብናል፡፡
ስለሆነም የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ መንግስት ታሳሪዎቹን ለማሰር ያበቃው ተጨባጭ ማስረጃ ካለ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ፤ ያ ካልሆነ ግን እስረኞቹን በአስቸኳይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቅ እናሳስባለን፡፡
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ

ሠማያዊ ፓርቲ የነፃነት ትግልና የሃበሻ ጀብዱ

April 28, 2014
በቅርቡ የሴቶችን ቀን አስመልክቶ በተደረገ የሩጫ ዝግጅት ወቅት የሚኒሊክና የጣይቱ ልጆችነ ነን ያሉ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች “አትለያዩን! አትከፋፍሉን! ነፃነት እንሻለን! ለድሃው ይታሰብለት! ኑሮ ከበደን! ውሃ ጠማን! መብራት ናፈቀን!” በማለት በጣም ሰብዓዊና እናታዊ ጥሪ ጮክ ብለው አሰምተው ነበር። ይህም መልካም ድርጊታቸው ለፍትህና ለአንድነት የሚደረግ ህዝባዊ ጥሪ በሚያስበርግጋቸው የወያኔ ባለስልጣናት ሁከት ፈጠራ ተብሎ ተወነጀሉ። ፕሮፌሰር አልማርያም በተቆጣው ብዕራቸው

… ያገሬ ወይዛዝርቶች በምህረት አልባ ጨካኞች ሲንገላቱና ሲወገሩ ከዳር ቆሜ ማየትን ህሊናዬ ፈጽሞ አይፈቅድልኝም። ይልቁንም የእንግልታቸው ምክንያት ሰብዓዊ በሆነው መብታቸው ድምፃቸውን ስላሰሙ በመሆኑ የነሱና የመሰሎቻቸውን ጥሪ በዚህም ሳቢያ የሚደርስባቸውን አበሳ ሁሉ ለአለም አሳውቅ ዘንድ ድምጼን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ…

ብለው ነበር። ከርሳቸው ድምጽ ጋር በማበር የሚያስተጋቡ ድምጾች ይኖሩ ዘንድ እውነት ነውና የኔንም ድርሻ እነሆ እጮሃለሁ። ጩሀቴም ቀደም ሲል በግፍ ለታጎሩ የህሊና እስረኞችና ሰሞኑን ለታፈሱት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና ደጋፊዎች አንዲሁም ለጎበዞቹ የዞን ዘጠኝ የሕዝብ አፈቀላጤዎችም (ብሎገሮችም) ነጻነት ያለኝ ጽኑ ፍላጎት መገለጫ ነው።
ሁከት ማለት የሌሎችን ሰላም ማደፍረስ፥ አምባጓሮና ጸብ ማንሳትና ማነሳሳት፥ የንብረት ጥፋትና በሰዎች ላይ አካላዊና ስነልቦናዊ ጉዳትን ማስከተል ነው። እኒህ ወጣት ሴቶች ግን ከዚህ በተቃራኒው የተንገላቱት ሰላም አንዳይደፈርስና ህዝብ እንዳይጎዳ በስልጣን ላይ ያሉት መንግስታዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ሰላማዊ ጥሪ ነበር ያቀረቡት። የሀሰት ፕሮፖጋንዳው ሰለባ ያልሆነ በሙሉ ወጣቶቹ በአንድነትና በፍትህ የጸናች ሀገር ለመረከብ ከዚህ የበለጠ ቢያደርጉም ተገቢ ነው የሚል ይመስለኛል። የነርሱ አሳሪዎች በነርሱ እድሜ ጠመንጃ አንስተው መጥፎ ነው ብለው የፈረጁትን መንግስት ለመዋጋት ጫካ መግባታቸውን አለመርሳት ብቻ ሳይሆን እንደትልቅ ገድል በየመድረኩና በየመጽሀፉ ሲናገሩና ሲያስነግሩ እንሰማለን። ታዲያ የዛሬው ትውልድ ያውም እንደነሱ ሰው ለመግደል ጠብመንጃ ሳያነሱ ፍትህ አይጉዋደል ብለው በሰላም መጠየቃቸው እንዴት መጥፎ ሁኖ ነው ለእስርና እንግልት የሚዳርጋቸው? ማሰርንና አፈናን እንደ የስልጣን ዘመን ማራዘሚያ አማራጭ አድርጎ መውሰድ ከሚያስብ አእምሮ ሳይሆን በፍርሃት ከተዋጠና ለውጥ አይቀሬ መሆኑን መቀበል ካቃተው ደካማ ጭንቅላት የሚመጣ ነው። በአንጻሩም ነገ የነርሱ የሆነው ወጣቶች በፍርሀት ተገንዘው አረመኔዎች ሀገራቸውንና ተስፋቸውን ሲያጠፉባቸው በዝምታ ሊያዩ አይቻላቸውም።
ለዚህም ነው በወጣቶቹ የሠማያዊ ፓርቲ መሪዎችና ደጋፊዎች ላይ ያለኝን ጽኑ እምነት መግለጽ የምሻው። የወጣቶች መነሳሳት ለሁሉም ወገን ብርታትን የሚሰጥ ነው። የለገመ፣ የሰነፈና ተስፋ የቆረጠ ወጣት የሞላበት ሃገር ሕዝብ መቃብር አፋፍ እንደቆመ ለቀስተኛ ነው። ለቀስተኛ መቼም ቢሆን ስለሚቀብረው ሰው ከሚሰማው ሀዘን ባሻገር እርሱም ነገ ሙዋች መሆኑን እያሰበ ሙዋቹን አፈር እራሱን ትካዜ አልብሶ ተስፋን ሳይሆን ፍርሀትን ሰንቆ ይመለሳል። ሀገር ተስፋ በቆረጠና ሽንፈትን በጸጋ በተቀበለ ወጣት ከተሞላች ቀብርዋ ተቃረበ ማለት ነው። ስለዚህ የሀገራችን ወጣቶች ተስፋ የሰነቁ፣ የበረቱና በእውቀትና ስነምግባር የታነጹ እንዲሆኑ ሁላችንም የየአቅማችንን ማድረግ ይኖርብናል። የሀገራችን ሰዎች “እናት የሞተች ቀን በሀገር ይለቀሳል… ወንድም የሞተ እንደሁ በሀገር ይለቀሳል…. ሀገር የሞተ እንደሁ ወዴት ይደረሳል?” ይሉ የነበረው ያለምክንያት አልነበረም። እናም የዛሬን ወጣቶች ድርጊት ከቀድሞው የሃበሻ ጀብዱ (የሀበሻ ጀብዱ ከሚለው መጽሀፍ) ጋር ጣምራ ቅኝት ላደርግበትና ወጣቶችን ላደንቅበት መርጫለሁ።
ስለምን የሃበሻ ጀብዱን እንደመረጥኩ ግን እመለስበታለሁ። የጣልያኑም ወረራ ሆነ የባንዳ መራሹ ወያኔ አገዛዝ ለኢትዮጵያ የሚበጅ አይደለምና ሀገሪቱን ወደተሻለ መንገድ ለመውሰድ የሚደርገው ጥረት ኢትዮጵያውያን ነን ለሚሉ ሁሉ የህልውናና የነፃነት ፍልሚያ መሆኑ ግልጽ ሊሆን ይገባል። የሠማያዊ ፓርቲና የትግራይ ተገንጣይ ነን የሚሉትን አቅም በመፈተሽ መንደርደርያውን ማጎልበት ያስፈልግ ይሆናል። ይህም መድፍ ተኳሽና በአውሮፕላን መርዝ የሚርጭን የግራዚያኒን ጦርና ነጠላ ለባሽ ባለጎራዴ እግረኛን እነደማወዳደር ማለት ነው። ምንና ምን ታወዳድራለህ የሚሉ እንዲህ ብለው ሊሞግቱኝ ይችላሉ።
ሰማያዊ ፓርቲ የወጣቶች፣ ተገንጣዮቹ እድሜ ጠገቦች ፤ ሰማያዊ ፓርቲ ባዶ ኪስ፣ መንግስት ነን የሚሉት ደግሞ የሀገሪቱን ሃብት የግላቸው ያደርጉ ዲታዎች አዎ ምንና ምን? ሰማያዊ ፓርቲ ብእርና ወረቀት ፣ ወያኔዎች ባለታንክ፣ አውሮፕላን መድፍና መትረየስ ታጣቂዎች። እናም የማይቻል የሚመስለውን ይቻላል የሚሉ ወጣቶችና ሰው እንደዘበት መፍጨት የማይገዳቸው ‘ተራራ አንቀጥቃጮች’ እንደምን አድርገው መጋጠም ይችላሉ? በዚህ አይነት ንፅፅር ተስፋ የቆረጡት ወገኖች “ይቻላል!” ብለው የተነሳሱትን ወጣቶች “እንዲያው አርፈው ቢቀመጡ ነው የሚሻለው። በአጉል ወኔ ተነሳስተው ማለቅ ብቻ ሳይሆን እኛንም ያስጨርሳሉ። ጊዜው አሁን አይደለም” የሚል ምክር ቢጤ ሲሰጡ ይሰማሉ። የፖለቲካ መሪና ጠቢብ ነን የሚሉም “ለአሁኑ ወያኔ ስልጣን ላይ ቢቆይ ይሻላል” ሲሉ ተደምጠዋል አሉ።
እውነትም ብቸኛ ሃይል መመዘኛ ሁኖ የሚታየው የጠብመንጃው ቁጥርና የመግደል አቅም ከሆነ ያስፈራል። እውነታው ግን የሀይል ምንጭ የጠብመንጃና የጦር ጋጋታ ብቻ አይደለም። ከጠብመንጃ በላይ የዘላቂ ሀይል መሰረቱና የመጨረሻ ድል አጎናጻፊው እውነትና ፍትሀዊ ምክንያት ነውና።
ጊዜው ዛሬ አይደለም የሚሉትም መካሪዎች ጊዜው መቼ እንደሚመጣ ቢያሳውቁንም ደግ ነበር። ኬይንስ የሚባለው የምጣኔ ሀብት ምሁር እንዳለው “ከረጅም ጊዜ በሁዋላ ሁላችንም ሙዋች ነን።” ስለዚህም የዛሬውን ነጻነታችንን ተነፍገን በነገ ተስፋ ብቻ ተሸንግለን ግፍን በፀጋ እንድንቀበል መመከራችን ደግም አይደለም። ነፃነት ተነፍጎ፣ ፍትህን አጥቶ፣ በደልን ተሸክሞ ተስፋ ቢስም ሆኖ መኖር አይቻልም። በደል ሲበዛ በቃኝ ማለት የሰው ልጅ ትክክለኛ ባህርይ ነው። ቢሆንም በርካቶች “እግዜር ያመጣውን እግዜር እስኪመልሰው” ሲሉ ይደመጣል። እግዜር የሌለውን አመል አውጥቶ ጥላቻ ቢለማመድ እንኳን እነዚህ አረመኔ ወንበዴዎች ለዚህን ያክል ጊዜ አናታችን ላይ ሁነው እንዲጨፈጭፉን አያዝብንም።
ፍትህና ነጻነት የሚገኘው በፀሎትና ልመና ብቻ ቢሆንማ ኖሮ አውሮፓውያን ሰሜን አሜሪካ ዘልቀው ሀገሬውን በበሽታና ረሀብ ሲጨፈጭፉት፣ እግዜሩ ዝም አይልም ነበር። አዎን እሱ መሬት ወርዶ ፍርድ የሚሰጥ ቢሆን አውሮፓውያን ጥቁር አፍሪካን ባርያ አድርገው በገዛ ምድሩ ላይ የግፍ ግፍ እየፈጸሙበት የእግዜርን ስም እየጠሩ መስቀልና መጽሀፍ ቅዱስ ይዘው ሲያስገበሩት ዝም ባላለ ነበር። ስለዚህም ነው ለነጻነት ሲባል ታንኩንም መትረየሱንም እንደነ አቡነ ጴጥሮስ መጋፈጥ የግድ የሚሆነው። ጸሎት ለብርታት ጥሩ ነውና ባይሆን እመብርሃን ለልጅሽ በደሌን እንደኔ ሆነሽ ንገሪልኝ ማለት፣ አላህንም ልጆችህ መከራችንን ከትከሻችን አሽቀንጥረን እንጥል ዘንድ ጉልበትና ብልሃት ጀባ በለን እያሉ መለማመን ጥሩ የሚሆነው። ግን ለብቻው በቂ አይደለምና ወጣቶች እንደ የግል ሀይማኖታቸው እያመለኩ እንደ እምነታቸው በጋራ ለነፃነት መታገላቸው የሚያበረታታንም ለዚህ ነው።
አሁን የሃበሻ ጀብዱን ለምን እንደጻፍኩ ላስረዳ አዎን የጣልያን ጀነራሎችን ሹምባሾችና አስካሪዎችን አስታውሼ መሆን አለበት። ታንኩንም፣ አውሮፕላኑንም መድፉንም መትረየሱንም ጭምር። የባንዳ ውርንጭሎችን፣ ልጆችና የልጅ ልጆችንም እንዲሁ አስቤያቸው ነው።
እነዚህ ነጠላ ላባሽ ባዶ እግር ተጓዥ ኢትዮጵያውያን በጣም የሚገርሙ ነበሩ። ኩራታቸውና በራሳቸው የመተማመን አቅማቸው ለውድድር አይመችም። እንደ ሀይል አሰላለፍ ቢሆን ከጣልያን ጋር ደፍሮ መጋጠም ከሞኝነት አይቆጠርም ትላላችሁ? ካላቸው የመሳርያና የወታደር ብዛት፣ ሰልጥኛለሁ የሚለው የነጩ ዓለም ያለው ጉልበትና ስልጣኔን የሚያውቅ ሰው በባዶ እግሩ ታንክ መግጠም ሞኝነት ነው ቢባል ማመን ብዙም ላይከብድ ይችላል። ለነርሱ ማን አልተንበረከከምና? ማንስ ቅኝ ግዛት አልሆነምና! ግን ኢትዮጵያ ምድር ላይ ታንክ በጎራዴ ድል ሆነ። አንዴ ቢሆን እድል እንለዋለን ሁለቴ ሶስቴም ሆነ። ሁለቴም ሶስቴም ነጠላ ለባሽ በባዶ እግር የሚጓዝ እግረኛና ቆመህ ጠብቀኝ ምንሽር ባለአውሮፕላንና ባለታንኩን ድል ነሱት። ግን ይህ አሸናፊነት እውን የሆነው ትክክለኛ ስነልቦና፣ አልገዛም አልንበረከክም የሚል እምቢ ባይነት ስለነበረ ነው። ለነፃነቱ ቀናዒ መሆን ከዚያም በላይ ወንድም የወንድሙ ተበቃይ መሆኑን ነበር። አይዞህ ባይና አጋር አብራ በረሃ ለበረሃ የምትጓዝ ጓድም ነበረችው። እሷን ማሳፈር ለባርነትም አሳልፎ ከመስጠት ሞቱን ይመኝ ስለነበር ነው። ሴቲቱም ብትሆን እርሱ ለነጻነቱ ሞቶ ግን የርሱን የጀግናውን ስም ይዘው ትውልድ የሚቀጥሉት ልጆቻቸው በነፃነት ቢኖሩ ምርጫዋ ስለነበረ ነው። የሴቶቹ ጀግንነትና ድፍረት ለወንዶቹም መነሳሳትና መበረታት ምክንያት ይሆናቸው ስለነበረ ነው የሚል ሃሳብን ነበር የሃበሻ ጀብዱን የጻፈው ፈረንጅ አዶልፍ ፓርለሳክ የዘገበው። “እነዚህ ነጠላ ለባሽ እግረኞች ይላል አዶልፍ ፓርለሳክ በጠላት መትረየስ አስሩ ሲወድቁ ሃያው ወደፊት ይገፋሉ ሃያው ሲወድቁ ሃምሳው ወደፊት ይገፋሉ ለሞት እየተጋፉ ወደፊት ይገሰግሳሉ እናም ያሸንፋሉ” ብሎ ሺህ ጊዜ አድናቆቱን መሰከረላቸው። እርግጥም ፍርሃቱን ያሸነፈ ጀግና ነው! እንዲያውም ነገስታቱ ወይም መሪዎቹ እየገቷቸው እንጂ ጣልያንን ድባቅ እየመጡ ቀይ ባህር ሊከቱ የሚችሉ ጎበዞች እንደሆኑ ሲጽፍ ገድላቸው በዐይነህሊናው የሚታየው ይመስላል። ታድያ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ምን አገናኘው ሰማያዊ ሰላማዊ ትግል ነው ታንክና ጎራዴን ምን አገናኘው? ለሚሉ በሚከተለው አስተያየት የተነሳሁበትን ለመደምደም እሞክራለሁ።
ልክ ይህንን ታሪክ አስቀምጠው የነገሯቸው አዛውንቶች ያሉ ይመስል ባዶ እጃቸውን ነፃነት ወይም ሞት ያሉ ቆራጦች የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ጀግነው ተነስተዋል። ይህንን መነሳሳት ደግሞ በሚገባ አሳይተዋል። አምስት ሲታገትባቸው አስራ አምስት ሆነው ይተማሉ፣ አስራ አምስት ቢታገት አምሳ አምስት ይሆናሉ። ስለዚህ የነጻነት ፍላጎታቸው ካልሞተ ለነፃነት የሚያደርጉት ትግል እንደማይቆም ግልጽ ነው። አዎ በጎበዝ አለቃ ተደራጅቶ በባላባት በባላባት ተጠራርቶ የወጣው ጀግና እንደዚያ ነበር ነፃነትን የተቀዳጀው። ሰማያዊ ፓርቲም መሪው ሲታሰር ሽባ የሚሆን ጥቂት አባላት ቢታገቱ የሚሽመደመድ እንዳይሆን ሆኖ የተደራጀ ይመስላል። እንደዚያ ሆኖ ሊጠናከርም ይገባዋል። ወጣት ወጣት የሚሸት እንቅስቃሴ ተስፋ ይሰጣል። ነቅተው ሌሎችንም የሚያነቁ፣ ጎብዘው ሌሎቸንም የሚያበረታቱ በዘርፈ ብዙው ትግል ውስጥ ብዙሃኑ እንዲሳተፉ ያበረታታሉ። ለዚህም ነው ታስረው ታስረው የማያልቁ… ከጎንደር መልስ አዲሳ አበባ፣ ከአዲስ አዋሳ እያሉ ሺህ ሚሊየን ወጣቶች ለነፃነትና ለክብር ሲቆሙ የምናየው። ያኔ በጠላት ወረራ ጊዜ አቢቹ የሚባል ለጋ ወጣት ነበር በወንድሞቹ ሞት ማግስት ጨርቄን ማቄን የማይሉ 200 ጎበዞች ብቻ ስጡኝ በማለት የራሱን ጦር ሊመራ ወሰነ። የርሱ የነበሩ በሬዎችን አሳርዶ የወንድሞቹን ተዝካር አወጣና ወደ ደፈጣ ውጊያም ገባ። ያ ወጣት ለጣልያን ያደሩ የትግራይ ሽፍቶችን ጨምሮ ጣልያኖችን አርበደበዳቸው። የ16 አመት ወጣት ምንም የጦር ስልጠና ያልነበረው ጀግና ሰልጥነናል ያሉትን መግቢያ መውጫ አሳጣቸው። ምንም እንኳ ከጀግኖቹ ተርታ ስሙን ሊናገሩ ያልፈለጉ ቢኖርም እንኳ ዛሬ ታሪኩ ታውቆ ወደፊትም ሲነገርለት ይኖራል። የዛሬዎቹ ወጣቶች በውል የሚያውቁት ወያኔን ብቻ ነው። ወያኔ ጸረ ኢትዮጵያ ፕሮፓጋንዳውን በሚነዛበት ሀገር ነው ያደጉት። ይሁን እንጂ የማይሞተው ኢትዮጵያዊነትና የነጻነት ጥያቄ አነሳስቷቸዋል። ዛሬም ብዙ አቢቹዎች ይኖሩናልና የወጣቶች መነሳሳት የነፃነት ብስራት ነው ስንል ከጎናችሁ አለን እያልናቸውም ነው። ሞት እስርና እንግልት ሌሎችን ወደፊት ያመጣል። ትግሉ ስልጣን መያዝ አይደለም ስልጣን በሰላማዊ መንገድ የሚያዝበትን የእኩልነት የነፃነት ብስራት የሚሰበክበትንና በተግባርም የሚረጋገጥበትን ጎዳና መቀየስ ነውና ለዚህ ቅዱስ ዓላማ አሁን ተመሳሳይ ዓላማ አለን የሚሉ በተለያየ የትግል ስልት ግን ለነፃነት ለሚታገሉ ሁሉ ብርታትና መነሳሳትን ይፈጥራሉ። ኢትዮጵያ ከጎጠኛ ወራሪዎችና አገር አፍራሾች ነፃ እስክትሆን ድረስ ትግሉ ይቀጥላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ።

Tuesday, 15 April 2014

የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ሚና በተመለከተ በኖርዌይ ኦስሎ ሕዝባዊ ውይይት ተካሄደ

April 14, 2014
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
Ginbot7 meeting in Norway
በዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ  የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት አፕሪል ቅዳሜ 12/2014  በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ  የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ተሳትፎ በተመለከተ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ተካሄደ:: በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ የሚጠጉ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች ከኦስሎ እና ከተለያየ ከተማ በመምጣት በስብሰባው ላይ የተገኙ ሲሆን  የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ በመሆን ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል::
ሕዝባዊ ስብሠባው በኖሬጅያውያን የሰአተ አቆጣጠር ከቀኑ 15:00 እስከ ምሽቱ 21:00 ሰዓት የተካሄደ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አቢ አማረ በኢትዮጵያ ውስጥ በወያኔ አረመናዊ ስርአት በጭካኔ በግፍ ለተገደሉ እና በተለያዩ አስር ቤቶች በፖለቲካ ኣስተሳስባችው ምክንያት ያለወንጀላች የሚስቃዩ ውድ ኢትዮጵያዊን ወገኖቻችን በማስብ  በዚሁ ዘረኛ ቡድን አስቃቂ የኣካል ጉዳት ለተፈጸባቸው ኢትዮጵያዊን  የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት በማስደረግ ስብሰባውን አስጀምረውታል::
በመቀጠለም አቶ ዮሀንስ አለሙ የዴምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሊቀመንበር የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸው ስለ ዲምክራሲያዌ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አመሰራረት እና ስለ ድጋፍ ድርጅቱ አላማ በማብራራት የድጋፍ ድርጅቱ በአሁኑ ሰአት በሀገር ቤት በሰላማዊ ትግል የወያኔን መንግስት ለመጣል እየታገሉ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶችን እየረዳ እንደሚገኝ እና ከሀገር ውጭ ደግሞ የወያኔን መንግስት  በሁለገብ ትግል  ለማስወገድ እየሰራ ያለውን የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ የፖለቲካ ድርጅትን በግንባር ቀደምነት እየረዳ እንዳለ በመግለጽ  የወያኔን ዘረኛ ስርአት ለመጣል ሁሉም ሰው አስተዋጿ ማድረግ እንደሚጠበቅበት እና ማንኛውም  ኢትዮጵያዌ ዜጋ በሀገራችን የጋራ ጉዳይ ስለሆነው  የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ሀሳብ በመለዋወጥ ፣በመካከላችን ያሉትን ማንኛውንም የሃሳብ ልዩነቶች ወደ ኋላ በመጣል ፣ በመቻቻል፣ ሀገር እያፈረሰ እና ሕዝብ እያዋረደ ያለውን የዘረኛውን የወያኔን መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሁለገብ ትግል ለማስወገድ መረባረብ እንዳለበት አጽኖት ሰጥተው ንግግር አድርገዋል::
Ethiopians public meeting in Norway
በመቀጠለም ዲምክራሲያዊ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ድጋፍ ከሚሰጣቸው ድርጅቶች መካከል አንዱ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል የሆኑት አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ ሰፊውን ጊዜ በመውሰድ ከንጉሱ ስርአት ጀምሮ በደርግ መንግስት ዘመንም በሀገራችን የተደረጉ የፖለቲካ ንቅናቄዎችንና ለውጦችን አንድ በአንድ በመዘርዘር አሁን ካለው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ጋር በማነጻጸር ሰፋ ያለ ትንታኔ ያቀረቡ ሲሆን አሁን ላይ ሀገሪቱን እየመራው ነው የሚለው የወያኔ መንግስት ከዚህ ቀድሞ ኢትዮጵያን ከመሩት ከሁለቱ መንግስታቶች ማለትም ከንጉሱም ከደርግም መንግስት ጋር ሲነጻጸር ፈጽሞ እንደማይገናኝ የወያኔ መንግስት ዘረኛና የዘረኝነት ፖለቲካ እያራመደ ያለ አረመናዊ መንግስት እንደሆነ አብራርተዋል::
የግንቦት 7  የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ አክለውም ከወያኔ በፊት የነበሩ ሁለቱ መንግስታቶች ለውድቀት የዳረጓቸውን ምክንያቶች በመጥቀስ የወያኔን አንባ ገነናዊ መንግስት ለአፋጣኝ ውድቀት ሊዳርጉት ይችላሉ የሚሉትን ግልጽ ምክንያቶች በመዘርዘር አስቀምጠዋል:: አቶ ቡዙነህ በሁለት የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በማንሳት እና በማብራራ ከሕዝብ ውይይት እንዲያደርጉበት ለመወያያ ያቀረቡ ሲሆን እነዚህም:
1, በሙስሊሙ ማህበረሰብ እና በወያኔ መካከል ያለው ግጭት
2, የህዳሴ ግድብን  በማስመልከት ያለው ተቃውሞ
ስለሙስሊሙ ማህበረሰብ ተቃውሞ ሲናገሩ የሙስሊሙ ትግል በሁለት አመታት ውስጥ የተደረገው ሰላማዊ ትግል በጣም የተሳካና ወያኔ በቀላሉ ሊያዳፍነው ያልቻለው ሰላማዊ መብትን የመጠየቅ ትግል እንደሚያደንቁ በመናገር ነገር ይህ በሙስሊም ማህበረሰብ በኩል እየተደረገ ያለው ትግል እስከ አሁን ድረስ ከመንግስት በኩል ምንም አይነት መልስ ሊያገኝ እንዳልቻለ እና ወደፊትም ከወያኔ መንግስት በኩል ምንም አይነት መልስ ያገኛል የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል:: ለዚህም ማስረጃው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ከጠየቋቸው አራት የመብት ጥያቄዎች አንዱም ካለመመለሱ በተጨማሪ እስካሁን መሪዎቻቸውም በሃሰት ውንጀላ በእስር እየማቀቁ ያለፍርድ እየተንገላቱ መሆናቸው ነው::
ነገር ገን አሁን እየሆነው ባለው ሁኔታ በእንደዚህ አይነት መንገድ እስከመቼ ድረስ የሙስሌሙ ትግል ይቀጥላል በማለት የተናገሩ ሲሆን አሁን እየሄደ ባለው አካሄድ የሙስሊሙ ተቃውሞ የትግል አቅጣጫውን እስካልቀየረ ድረስ ረጅም ርቀትን ትግሉ ሊቀጥል ይችላል የሚል እምነት እንደሌላቸው እና ነግር ግን የሙስሊሙ ጥያቄ ከእምነት መብት ጥያቄ ባሻገር ወደ የዜግነትን መብት ወደ ማስከበር መለወጥና መሸጋገር  እናደለበት በመናገር የሙስሊሙ ማእበረሰብ ጥያቄ ፍሬ ሊያፈራ የሚችለው  ትግሉ በዚህ መልኩ ሲቀጥል እንደሆነ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰተዋል::
በሁለተኛም የህዳሴ ግድብ በሚመለከት  ያቀረቡት ሀሳብ ወያኔ የራሱን የፖለቲካ ኪሳራና በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለዉን ግፍ በዕድገት ስም ለመሸፈን ያመጣዉ እንጂ ታቅዶበትና ለህዝቡ በማሰብ እንዳልሆነ በኢትዮጵያና በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለዉ ግፍ እንደ ማስረጃነት በማቅረብ ያብራሩ ሲሆን እንደ ምሳሌም ወያኔ ሃገራዊ የሆነ አላማ ይዞ ካለመነሳቱ አንፃር የሃገርን ድንበር አሳልፎ እስከመስጠት እየሄደ ያለበትን ሁኔታ ጠቅሰው ይህ አሰራር ደግሞ የዲክታተሮች ባህሪ እንደሆነ አብራርተዋል::
የወያኔ መንግስት በህዳሴ ግድብ ሰበብ ምክንያት በማድረግ በመላው አለም ኢትዮጵያኖች በሚኖሩበት ሀገሮች በመዞር የዲያስፖራውን ቀልብ ለመውሰድ የሚያደርገው የአባይ ቦንድ ሽያጭ ሩጫ በዲያስፖራ ተቃዋሚዎች አማካኝነት በፍጹም እንዳልተሳካለት ይህንንም የወያኔ በአባይ ቦንድ ሽያጭ ስም ገንዘብ ዘረፋ በመቃወም ወያኔን አሳፍረው ከመለሱት መካከል በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች እንደሆኑ በማስታወስ  የዚህ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሰበብ የወያኔን መንግስት ወደ መጥፎ ውድቀት ላይ ሊጥለው እንደሚችል በማመን የወያኔ መንግስት በአሁን ሰአት ከግብጽ መንግስት ጋር እየገባ ያለው ሰጣ ገባ ለኢትዮጵያ መጥፎ ሊሆን እንደሚችል በመግለጽ ንግግራቸውን አጠቃለዋል::
በመቀጠልም አቶ ብዙነህ ባነሷቸው ነጥቦችና እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ከስብሰባው ተሳታፊዎች ለቀረበላቸው በርካታ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ሰፋ ያለ ውይይትም ተደርጓል፥፥ ከውይይቱም በማስቀጠል የዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ዳንሄል አበበ የዲምክራሲያዌ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የአቋም መግለጫ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ድርጅታቸው ወያኔ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍና በደል ፈጽመው እንደሚያወግዙ እና ዴምክራሲያዌ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሁል ጊዜ ከግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ ጎን እንደሚቆም ቃል በመግባት የአቶ ቡዙነህ ፅጌን በኖርዌይ በመገኛት ለህዝቡ ለሰጡት ገለጻ አመስግነዋል::
በዝግጅቱ መጀመሪያና ማጠቃለያ ላይ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል መዝሙር በመዘምራን የተዘመረ ሲሆን በየጣልቃው የተለያዩ የባህል ዘፈኖች በተወዛዋዦች ታጅቦ የቀረበ ሲሆን ጣእም ያለው ባህላዊ ምግብም በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የሴቶች ክፍል ተስተናግዷል፥፥ ስብሰባውን ተጀምሮ እስኪያልቅ አቶ ፍቅሬ አሰፋ መርተውታል::
በመጨረሻም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ለዝግጅቱ መሳካት የበኩላችሁን ላበረከታችሁና ከተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች ረዥም ርቀት በመጓዝ የዝግጅቱ ታዳሚ ለነበራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን እና እንዲሁም የድርጅቱ አባላቶች ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን::
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ

በኖርዌ ያሉ ኢትዮዽያውያን የወያኔን የስለላ መረብ በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

April 14, 2014
Ethiopians demonstration in Norway
በ11-4-2014 በኖርዌ ያሉ ኢትዮዽያውያን የወያኔን የስለላ መረብና ኖርዌ በስደተኛው ላይ ያላትን ፖሊሲ በመቃወም    የተቃውሞ ሰልፍ አረጉ።  23 ዓመት እራሱ መራጭ እራሱ ተመራጭ ሆኖ በጠመንጃ አፈሙዝ ህዝቡን እያንቀጠቀጠ የኖረው ወያኔ አንድ ቀን ሕዝብ በቃኝ ብሎ አንቅሮ እንደሚተፋውና ንብ ሆኖ ለነፃነቱ እንደሚነሳ ማወቅ ነበረበት።
ግን አልሆነም ዜጎች እንደዜጋ በሐገራቸው መኖር ቀርቶ በስደትም ሰላማቸውን ማግኘት አልቻሉም።
እስርና እንግልት፣ረሐብና ሰቆቃ፣ስደት የእያንዳንዱ እጣ ፋንታ ሆነ፤በወያኔ ዘመን ሰው ብቻ አይደለም መሬትም መሰደድ ጀምሮ የግል ጥቅሙን ለማስጠበቅ ሲል የኢትዮዽያን ለም መሬት ለሱዳን በመሸጥ ላይ ይገኛል
ኢትዮዽያንና ኢትዽያዊነትን ያሉ ሁሉ አሸባሪ እየተባሉ በየእስርቤቱ ታጉረው እጣ ፈንታቸው እስርና እንግልት ሆነ ሐገራቸውን ጥለው በባሕርና በየብስ አቆራርጠው የሞተው ሞቶ የተረፈው በአለም ዙሪያ ተበትኖ ጥገኝነት  በመጠየቅ ይኖራል::
በዚሕም የተሳካላቸው ጥቂቶች ሲሆኑ ባብዛኛው ወያኔ ለውጩ አለማት በሚያሳየው ሁለተኛው ፊቱ ምክንያትና ምእራባውያን ከሐገሪቱ ከሚያገኙት ጥቅም የተነሳ ሐገርህ ዲምክራሲ ነው እየተባለ ፍትሀዊ ያልሆነ መልስ እየተሰጠው በመጉላላት ላይ ይገኛል።
ያም ሆኖ የሐገሩ ጉዳይ በደም ስሩ ሰርጎ የገባው ኢትዮዽያዊ ሁሉ ጠዋት ማታ ኢትዮዽያዬ እያለ ይጮሀል። ይህ የህዝብ ቁጣ ያስፈራው ወያኔ ያለ የሌለ የሐገሪቱን ኢኮኖሚ እየመዘበረ ዜጎችን ይሰልላል ያሰልላል፣አልፎ ተርፎም ዜጎችን ከመሰሎቹ ጎረቤት ሐገሮች ድረስ በመሄድ ጎትተው እስርቤት ያስገባሉ።
ይህንን ለመቃወምና ለማውገዝ ነበር የኢትዮዽያ ስደትኞች ማህበር በኖርዌ ሰላማዊ ሰልፍ አዘጋጅቶ ኢትዮዽያውይኑ ዛሬም ስለ ሐገራቸው ሊጮሁ የወጡት፤ ሰልፈኞቹ ድምፃቸውን እንዲህ በማለት ነበር ድምፃቸውን ያሰሙት እኛ ስደተኞች እንጅ ወንጀለኛ አይደለንም፣ኖርዌ ለማፊያው ወያኔ የምታደርጊውን እርዳታ አቁመሽ ከኢትዮዽያ ሕዝብ ጋር ቁሚ፣ወያኔ የሚያደርገውን ተግባር እናወግዛለን፣ሼም ኦን ዩ ሳውዝ ሱዳን ኦኬሎን አሳልፈሽ የሰጠሽ፣ወያኔ አሸባሪ ነው፣ለውጥ እንፈልጋለን፣ኖርዌ የዩኤንን ህግ ታክብር የሚሉትን የመሳሰሉ ሲሆን
በሰልፉ ላይ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅት ተወካዮች መልክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን የኢትዮዽያ ዲሞክራሲያዊ ለውጥ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ተወካይ አቶ ዳንኤል የወያኔን ጀሌዎች የማጋለጡ ስራ በሚገባ እየተሰራበት መሆኑን ሲገልጡ ሰልፈኛው በጭብጨባ የተቀበላቸው ሲሆን የስደተኛ ማህበሩም ተወካይ ኖርዌ ነፃ እንድታወጣን ሳይሆን ለወያኔ የምትሰጠውን እርዳታ አቁማ ድጋፍ እንድትሰጠን ነው፤ በተጨማሪም ኖርዌ አቶ ኦኬሎን ታስለቅቅ በማለት  ተጠይቃለች። በሰልፉ ላይ የኖርዌ ሊብራል ፓርቲ ተወካይ ከሰልፈኛው ደብዳቤ ተቀብለው መልክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን የኖዋስ ፣አንቲረሲስት ተወካዮችም እንዲሁ ይዘውት የመጡትን መልክት ለሰልፈኛው አስተላልፈዋል።
ከዚያ በቀጥታ ወደሶፊን በርግ ሎካል አዳራሽ ሰልፈኛው አምርቶ ምሳ  ከተበላ በሁዋላ ኮሚቴው ካባላቱ ጋር ሰፊ ዉይይት ያደረገ ሲሆን የ፫ወር የስራ ሪፖርትም አቅርቦአል።
የኢትዮዽያ ስደትኞች ማህበር በኖርዌ

Friday, 11 April 2014

..ሰበር ዜና፣ የሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ

April 11, 2014
ሰሞኑን አንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ የሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ህወሃት/ኢህአዴግን በደብዳቤ ሲያስፈቅድና ፍቃድ ሲከለከል፣ ከዚያም ድግሞ ለሌላ ጊዜ ሲያስተላልፍ የተላለፈውን ቀንም መልሶ ሲሰርዝ በመጨረሻም ቀኑን ወደፊት እንደሚያስታውቅ ገልጾ ነበር ጉዳዩን በእንጥልጥል የተወው።
ይህ በዚህ እንዳለ የሰማያዊ ፓርቲ በፌስ-ቡክ ገጹ ላይ የሚከተለውን ጥሪ አስተላልፏል፣
———————————–

የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልሳለን!!!

የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልሳለን በሚል መሪ ቃል ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 እሁድ ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ከጠዋቱ 4 ሰአት እስከ 8 ሰኣት ድረስ በጃንሜዳ ያደርጋል፡፡

Semayawi (Blue party) called rally in Addis Ababa

በኢትዮጵያ የመብቶች ትግሎች ሁሉ ህወሓትን ከሥልጣን ወደ ማስወገድ አቅጣጫ ያመራሉ! (ግንቦት 7)

April 11, 2014
Ginbot 7 weekly editorialየሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎች የክስ ሂደት በበርካታ አሳዛኝ ጉዳዮች የታጀቡ ቢሆኑም የሚሰጡት ትምህርት ግን ከፍተኛ ነው። እነዚህ ወገኖቻችን “ችሎት” በተሰኘው የአገዛዙ የድራማ መድረግ በመገኘት ፍትህን ለመግደል ካባ ለብሰው “ዳኞች” ተብለው ለተኮፈሱ የአገዛዙ ተላላኪ ካድሬዎች እና ለመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ያደረጓቸው ጠንከር ያሉ ንግግሮች ካድሬ “ዳኞችን” አሳፍረዋል፤ ኢትዮጵያዊያንን ግን አኩርተዋል። እኚህ ወገኖቻችን ከወያኔ ችሎት ፍትህ ይገኛል የሚል ብዥታ ባይኖራቸውም መድረኩን መልዕክት ለማስተላለፊያነት ተጠቅመውበታል። በዚሁ መድረክ በአገዛዙ እጅ ከወደቁበት ጊዜ ጀምሮ እየደረባቸው ስላለው ሰቆቃ ሲናገሩ አድማጮች ሊቆጣጥሩት የማይችሉት ሐዘንና እልህ ውስጥ እንዲገቡ አድርጓቸዋል።
ወያኔ እንዲህ ዓይነቱ ጭካኔ የሚፈጽመው በሙስሊም መሪዎች ላይ ብቻ አይደለም። የህግ እውቅና የተሰጣቸው መብቶቻቸው እንዲከበርላቸው በጠየቁ ወገኖቻችን ሁሉ ተመሳሳይ ሰቆቃ ሲፈጸም ኖሯል፤ አሁን እየተፈጸመ ነው። “ኑሮ ከበደን” ያሉ ወጣቶች ተደብድበዋል። “የእርሻ መሬት አጣን” ያሉ ገበሬዎች ከያዙት ቁራሽ መሬት ተፈናቅለዋል፣ ተግዘዋል፣ ከነልጆቻቸው ለጎዳና ኑሮ ተዳርገዋል። በሀረር እና በአዲስ አበባ ከተሞች እንደታየው “ነግደን እንኑር” ባሉ ነጋዴዎች ላይ ከአቅም በላይ ከሆነ ግብር ጀምሮ በንብረታቸው ላይ እሳት እስከመልቀቅ የደረሰ አረመኔዓዊ ድርጊት ተፈጽሟል።
በዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ አንቀጽ 18 መሠረት እያንዳንዱ ሰው በግሉም ሆነ በጋራ የፈለገውን ሃይማኖት የመከተልና የማስተማር፤ ያልፈለገውን ደግሞ የመተው መብት አለው። ስለሆነም የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ተግባራት በዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ እውቅና ለተሰጣቸው መብቶቻቸው መከበር ያደረጉት ትግል ነው። ለወጉ ያህል “ሕገ መንግሥት” ተብሎ በሚጠራው ኢትዮጵያዊያንን ለመክሰሻነት ብቻ በሥራ ላይ በሚወለው ሰነድ ውስጥ የተካተቱ ቢሆንም ዓለምዓቀፍ እውቅና ያገኙ መብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ ተረግጠዋል። ለእነዚህ መብቶች መከበር በጽናት የቆሙ የኢትዮጵያ ውድ ልጆች ከተራ የመንደር ካድሬና ጆሮ ጠቢ እስከ እስከ ከፍተኛው እርከን ባለ ባለሥልጣኖች ተዋክበዋል፤ ሰቆቃ ተፈጽሞባቸዋል።
ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ለእምነት መብቶቹ መከበር እስካሁን ያደረገው ተጋድሎ የሚደነቅ ነው። የተቀናጁ እንቅስቃሴዎቹ፣ ተምሳሌታዊ የተቃውሞ ምልክቶች አጠቃቀሙ የሚያበረታታ ነው። ክርስቲያኑ ከዚህ የሚማራቸው በርካታ ቁም ነገሮች አሉ።
ከሙስሊም እንቅስቃሴና ወያኔ ይህንን እንቅስቃሴ ለማፈን እየሰዳቸው ካሉ እርምጃዎች የምንረዳው አንድ ትልቅ ሐቅ የቱን ያህል ጨዋና የሰለጠነ ቢሆን ወያኔ የሕዝብ ድምጽ ለማዳመጥ ፍላጎት የሌለው መሆኑን ነው። ሙስሊም ወገኖቻችን ጥያቄዎቻቸውን በሚያስገርም ቁጥብ ሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) ቢያቀርቡም ከወያኔ የተሰጠው ምላሽ ግን አፈና፣ ረገጣ፣ ቶርቸር እና ከእስከዛሬዎቹ ይበልጥ አፋኝ የሆኑ ደንቦችና ድንጋጌዎችን ነው። ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ያደረጓቸው ትግሎችም እንደዚሁ ወደ ባሱ የመብት ጥሰቶች እያመሩ ነው። ከዚህ የምንማረው ነገር ትግሉ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂዎችን መፈተሽ እንደሚያስፈልግ ነው።
እንደሚታወቀው፤ ሰብዓዊ መብቶች እርስ በርሳቸው የተቆራኙ፤ እርስ በርሳቸውም የሚደጋገፉ ናቸው። አንዱ የመብት ዓይነት ሲጓደል፤ ሌላውም አብሮ ይጓደላል። ለምላሴ የመናገር መብት ተገፎ እያለ የማምለክ መብት ሊፋፋ አይችልም፤ ወይም ደግሞ ፍትሃዊ ዳኝነት የማግኘት መብት ተጥሶ እያለ የማምለክ መብትን የሚያስከብር ተቋም ሊኖር አይችልም።
ለመብቶች መከበር የሚደረጉ ትግሎች፤ በተለይም ደግሞ የሙስሊም ወገኖቻችን ትግል የደረሰበት ደረጃ በአንክሮ ሲጤን ስትራቴጂን በተመለከተ በጥልቀት ልናስብባቸው የሚገቡ በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውን እንገነዘባለን። ለጊዜው ሁለት ነገሮች ላይ አጽንዖት ሰጥተን እናልፋለን።
  1. ከላይ እንደተገለፀው የመብት ትግሎች ሁሉ መደጋገፍ ይኖርባቸዋል። ቀደም ሲል በባህርዳር፣ በኋላም በአዲስ አበባ በሴቶች ዓለም ዓቀፍ ቀን አሁን ደግሞ በደሴ ውስጥ እንደታየው የመብት ጥያቄዎች ሁሉ ተደጋግፈው መነሳት ይኖርባቸዋል። ይህ የመደጋገፍ ልምድ የሁለቱ ትላልቅ ሃይማኖቶች ተከታዮች ለየእምነቶቻቸው ነፃነት በሚያደርጉት ትግል ውስጥ መኖር ይኖርበታል። የሙስሊሞች የመብት ጥያቄዎች የክርስቲያኖችም፤ የክርስቲያኖች ደግሞ የሙስሊሞችም መሆን ይኖርበታል።
  2. በሥልጣን ላይ ያለው የህወሓት አገዛዝ አንዱንም የመብት ጥያቄ መመለስ የማይችል መሆኑ ግልጽ መሆን ይኖርበታል። በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ የመብት ጥያቄዎች ግብ ወያኔን ከሥልጣን ከማባረር ያነሰ መሆን አይችሉም። ስለሆነም የመብት ማስከበር ትግል ስናካሂድ ይህን አልመን እና ለዚህም ተዘጋጅተን መሆን ይኖርበታል። ይህ ደግሞ ከፍተኛ የስነልቦና፣ የድርጅትና የስልት ዝግጅት ይጠይቃል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር ህወሓት ከሥልጣን መወገድ ይኖርበታል ብሎ ያምናል። ወያኔ በሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ መገለል፣ መረገጥ፣ መጋዝ፣ መሰደድ፣ መደብደብ፣ የማይቀርልን በመሆኑ ሥቃያችንን ለመቀነስ ወያኔን ማስወገድ ይኖርብናል ብሎ ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። ከዚህ በተጨማሪ በተለያዩ መንገዶችና ምክንያቶች የምናደርጋቸው ትግሎች ወደ አንድ አቅጣጫ ያመራሉ ብሎ ያምናል። ትግሎቻችን ዞሮ ዞሮ ህወሓትን ከሥልጣን ወደ ማስወገድ ማምራታቸው ግልጽ ስለሆነ ለዚህ የሚያስፈልገውን ስነልቦናዊና ቁሳዊ ዝግጅቾችን እናድርግ ይላል።

የህወሓት ስትራተጂ: –

ማስፈራራት – በጥቅም መደለል- ማግለል- ማስቀናት- ከጥቅም ማገድ- ስም ማጥፋት- በመጨረሻ መፍራትና መሸነፍ!
==================
የህወሓት ዓላማ ስልጣን ነው። ስትራተጂውም ከዓላማው ይመነጫል። ስልጣን ላይ ለመቆየት የሚከተለው ስትራተጂ ሌሎች አማራጭ ፓርቲዎች በሐሳብና በተግባር በማሸነፍ (በልጦ በመገኘት) ሳይሆን አማራጭ ሐሳብ ያላቸው ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በማዳከም ነው። ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ለማዳከም የሚጠቀመው የመጀመርያ ስትራተጂ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን ማስፈራራት ነው። የፓርቲ አባላትን በማስፈራራት አባልነታቸውን (ተቃውሞአቸውን) እንዲያቆሙ ተፅዕኖ ይደረጋል።
የማስፈራራት ስትራተጂ ካልሰራ (የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በህወሓት ፕሮፓጋንዳ ካልፈሩ) በጥቅም የመደለል ስትራተጂ ይከተላል። የተቃውሞ ፓርቲ አባልነታቸው አቁመው ለህወሓት ከሰሩ (ተቃዋሚ ፓርቲዎችን እየሰለሉ ህወሓትን ካገለገሉ) ቁሳዊ ጥቅም እንደሚሰጣቸው ይነገራቸዋል። በመረጡት ቦታ መሬት ይሰጣቸዋል፤ የፈለጉትን ዓይነት አገልግሎት ያገኛሉ።
ይህንን በጥቅም የመደለል ስትራተጂ ካልሰራ (ድለላው ተቀባይነት ካላገኘ) የማግለል ስትራተጂ ይከተላል። ጓደኞችህን በማስፈራራት ካንተ (ፓርቲ አባል) እንዲርቁ ይደረጋል፤ ከማህበራዊ ህይወትህ ትገለላለህ። ብቸኝነት ተሰምቶህ ዓቋምህ ትቀይር እንደሆነ ለማየት ነው። መጀመርያ የደህንነት ሰዎች እየመጡ ጓደኞችህን ያስፈራራሉ። ከፈሩና ከተለዩህ ህወሓቶች ተሳካላቸው ማለት ነው። ካልፈሩ ደግሞ ቁሳዊ ጥቅም ይቀርብላቸውና አንተን በጥቅም የማስቀናት መንገድ ይከተላሉ። (ብዙ ጓደኞቼ ስለፈሩ ወደ ቁሳዊ ጥቅም የማግኘት ደረጃ ያልደረሱ አሉ፤ የተወሰኑ ግን በጣም ሃብታም ነጋዴዎች ሁነዋል፤ እንኳን ተጠቃሚ ሆኑ፤ ህሊና በቁስ ነገር መሸጥ መጨረሻው ፀፀት ቢሆንም)። በመጨረሻ አንተን ከሁሉ ዜግነታዊ ጥቅምና ሕጋዊ መንግስታዊ አገልግሎት ያግዱሃል። በዚህ ሁሉ ተፅዕኖ ካልተምበረከክ የደህንነት ሰዎች አሰማርተው ስምህ እንዲጠፋ የፈጠራ ወሬዎች ይነዛሉ። አሁን ካልተሸነፍክ ግን በቃ እነሱ ይፈሩሃል፤ ያከብሩሃል። በመጨረሻም እጃቸው ይሰጣሉ፤ ይምበረከካሉ። መሸነፋቸውን በገዛ አንደበታቸው ይመሰክራሉ።
ስለዚህ በግለሰብ ደረጃ ህወሓቶች ስትራተጂ: ማስፈራራት፣ በጥቅም መደለል፣ ማግለል፣ ማስቀናት፣ ከጥቅም ማገድ፣ ስም ማጥፋት ነው። በመጨረሻ መፍራትና መሸነፍ፤ ድል ያንተ ነው።
በፓርቲ ደረጃ: ተቃዋሚ ፓርቲዎች አማራጭ ሐሳባቸውን ለህዝብ እንዳያቀርቡ ይደረጋል። ስለነሱ መጥፎ ነገር ለህዝብ ይነገራል። ህዝብ ፖለቲካ እንዳያውቅ ይደረጋል፤ ምክንያቱም ህዝብ ፖለቲካ ካወቀ መብቱ ያውቃል። መብቱ ካወቀ ነፃነቱ ያውቃል። ነፃነቱ ካወቀ ዓፈና ይቃወማል። ዓፈና ከተቃወመ ዓፋኝ ስርዓትን ከስልጣን ያባርራል። ዓፋኝ ስርዓት ከስልጣን ከተባበረ ህወሓት ስልጣን ይለቃል። ምክንያቱም ህወሓት ዓፋኝ ስርዓት መሆኑ ይደረስበታል። ስለዚህ የህወሓት ጥረት ህዝብ እንዳያውቅ ማፈን ነው።
ለዚህም ነው የህወሓት ዋነኛ ስትራተጂ ህዝብን ማፈን የሆነው። ህዝብ ሲታፈን ዓፈናውን መጋለጥ አለበት። የህዝብ ዓፈና የሚያጋልጡ የግል ጋዜጠኞች ናቸው። ጋዜጠኞች በህዝቦች ላይ የሚደርስ ዓፈና በማጋለጥ የጋዜጠኝነት ግዴታቸውን ይወጣሉ። ህወሓት ዓፋኝ ስርዓት መሆኑ ስለሚያውቅ ህወሓት በህዝቦች ላይ የሚያደርሰውን ዓፈና ሊያጋልጡ የሚችሉ የግል ጋዜጠኞች በጥቅም ማማለልና መደለል ጀምሯል። በዚሁ መሰረት ብዙ የግል ጋዜጠኞች በመረጡት ከተማና ቦታ መሬት ይሰጣቸዋል። ለጋዜጠኞች መሬት የመስጠት ድርድር (ቅሌት) ተጀምሯል። በድርድሩ የተስማሙ ጋዜጠኞች መሬት ይሰጣቸዋል። እንደዉጤቱም በህዝቦች ላይ የሚደርስ ዓፈና ሳያጋልጡ ያፍናሉ። የዓፈና መረጃ ያፍናሉ ማለት ነው። ሙያቸው ይክዳሉ ማለት ነው። እስካሁን መሬት የተሰጣቸው ጋዜጠኞች አውቃለሁ። የተሟላ ስም ዝርዝር ከተወሰነ ግዜ በኋላ ይቀርባል።

በዚህ መንገድ ህወሓት በስልጣን የመቆየት ህልሙ ለማሳካት ጥረት እያደረገ ይገኛል። ህዝብን በማፈን ስልጣን ላይ መቆየት እንደማይቻል ከደርግ ስርዓት መማር አለመቻሉ ያሳዝናል። በስልጣን ለመቆየት የሚረዳ የህዝብ ይሁንታ ነው። የህዝብ ይሁንታ የሚለካው በምርጫ ነው። ምርጫ የሚኖረው ደግሞ የህዝብ ነፃነት ሲኖር ነው። ህወሓት በደህንነት ሰዎቹ ላይ የተንጠለጠለ ህዝባዊ መሰረት የሌለው ዓፋኝ ስርዓት ሆነዋል። ከስር መሰረቱ እንደሚነቀል በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል።

ዜና ዕረፍት: የአሞራ አባት በድንገት አረፉ! – አብረሃ ደስታ በፌስ ቡክ እንደዘገበው

የጀግናው “አሞራ” አባት አቶ ነጋሽ ገብረሩፋኤል መጋቢት 20, 2006 ዓም በ80 ዓመታቸው በድንገት ማረፋቸው ታውቋል። አቶ ነጋሽ ወንድ ልጆቻቸው ለህዝብ ነፃነትና ደህንነት ሲሉ የህይወት መስዋእትነት በመክፈላቸው ምክንያት የሚረዳ አጥተው ባላቸው ዓቅም ሰርተው ለመብላት ዕንጨት ሲቆርጡ ድንገት ወድቀው ተጎድተው ለሕክምና የሚደርስላቸው ወገን በማጣታቸው ምክንያት ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል። አቶ ነጋሽ በትግራይ ማእከላዊ ዞን ቆላ ተምቤን ወረዳ ኗሪ ነበሩ። የአሞራ የትውልድ ቦታ ቆላ ተምቤን በህወሓቶች ከተበደሉ ወረዳዎች አንዷ ነች። ያከባቢው ኗሪዎች “ዓረና” እየተባሉ የመንግስት አገልግሎትና መሰረተ ልማት ተነፍገዋል። ፍትሕ አጥተዋል።
የኢቲቪ ጋዜጠኞች በወረዳው አስተዳዳሪዎች ታጅበው ከአቶ ነጋሽ ጋር (ለፖለቲካ ጥቅም) ቃለመጠይቅ ለማካሄድ ወደ ቆላ ተምቤን ተጉዘው ጉሮሮ በምትባል ትንሽ የገጠር ከተማ ሲደርሱ የአቶ ነጋሽን ሕልፈት ሲሰሙ በስርዓተ ቀብሩ ሳይገኙ ተመልሷል። ህወሓት አቶ ነጋሽን የሚፈልጋቸው ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ ነበር ማለት ነው። የአቶ ነጋሽ ሞት በኢቲቪ አልተነገረም።
ህወሓቶች የልጃቸው አሞራን ታሪክና ጀግንነት ለፖለቲካ ፍጆታ ከማዋል ያለፈ ዕርዳታ አድርገውላቸው እንደማያውቁ ያከባቢው ኗሪዎች ገልፀዋል። የተሰው ልጆቻቸው መሬት በህወሓቶች ተነጥቀዋል። “አሞራ ፊልም” ሲሰራ አቶ ነጋሽ ቃለ መጠየቅና ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ቃል ተገብቶላቸው ሲያበቃ ለህወሓት መሪዎች ጥቅም ሲባል ቃለ መጠይቁ ሲካሄድ ለአቶ ነጋሽ የተደረገ ድጋፍ ግን አልነበረም። ይልቁንስ የልጆቻቸው መሬት ተነጥቆ ለሌሎች ካድሬዎች ተሰጥቷል።
ለፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ሲባል ስለ አሞራ ታሪክ ይተረካል። አሞራ ያን መስዋእት ከፍሎ በሆነ ተአምር በህይወት ተርፎ አሁን “ለዴሞክራሲና ነፃነት ነበር የታገልኩትና የፈለኩትን ፓርቲ እደግፋለሁ፣ ያልፈለኩትን ፓርቲ ደግሞ እቃወማለሁ” ብሎ ዓረናን ቢደግፍ ኑሮ ከሃዲ ተብሎ በህፃናት በድንጋይ ይወገር ነበር። አሞራ እንኳን ጓዶች ህን እነ ስየና አስገደ አላየኋቸውም። በቃ በል በሰላም ተኛ።
የአቶ ነጋሽን ነፍስ በገነት ያኑርልን። ለቤተሰቦቻቸውን ፅናቱ ይስጥልን። R.I.P

ስለፍትሕ ሲባል፤ ሥርዓቱ ይፍረስ! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ )

April 11, 2014
ባለፉት አራት አስርታት ሀገሪቱ አያሌ ተግዳሮቶችን መጋፈጧ ባይዘነጋም፤ በተለያየ ጊዜ ሚሊዮኖችን ካረገፈው አሰቃቂው ረሃብ በማይተናነስ መልኩ ሕዝቦቿን ዋጋ ያስከፈለ ጉዳይ ቢኖር የፍትሕ አለመከበር ያስከተለው ሁለንተናዊ ምስቅልቅሎሽ ነው ብሎ ለመናገር የሚያስደፍሩ በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡ የየካቲቱን አብዮት ጠልፎ ሥልጣኑን የተቆጣጠረው ወታደራዊው ደርግ፣ የፍርድ ቤት ደጆችን በጓጉንቸር ቆልፎ ሲያበቃ፣ የራሱ አባላት እጃቸውን እያወጡ ድምፅ በመስጠት በአፄው ባለስልጣናትንም ሆነ ግብረ-አበሮቹ በነበሩ መኮንኖች ላይ የሞት ቅጣትን ያህል የመጨረሻ ከባድ ውሳኔ የማሳለፍን አስደንጋጭ ክስተት ጨምሮ፤ ከከተማ እስከ ገጠር ያደራጃቸው የአብዮት ጠባቂዎችና የገበሬ ማሕበራት ከየቤቱ አንቀው እያወጡ “ነፃ እርምጃ” እንዲወስዱ፣ ከየእስር ቤቱ እየለቃቀሙ በጅምላ እንዲረሽኑ በአዋጅ የፈቀደበት ጊዜ የፍትሕ ምኩራቡ ፈርሶ በግላጭ የተቀበረበት ዕለት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በርግጥ ይህ የማን-አለብኝነት አረመኔያዊ አገዛዝ የታቃውሞውን ጎራ በማጠናከር ታሪካዊ ውድቀቱ እንዲፋጠን ካደረጉ ምክንያቶች አንዱ እንደነበር ለመረዳት 17 ዓመታትን መውሰዱ አይዘነጋም፡፡Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editor
“ፍትሕ አልባው አምባ-ገነናዊ የደርግ ስርዓት አማርሮ በርሃ ያስወጣንና ብሶት የወለደን የለውጥ ሃዋርያት ነን፤ በመቃብሩም ላይ ፍትሕ-ርትዕ የሰፈነባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንመሰርታለ” በማለት ከበሮ ይደስቁ የነበሩት የያኔው “ነፃ አውጪዎች”ም፣ ደርግ አፍርሶ የቀበረውን የፍትሕ ምኩራብ አመዱን አራግፈው ቢያነሱትም፤ ባነበሩት አስመሳይ ሥርዓት በኩል በዘውግ ማንነት፣ በሙስናና በሙያ አልባ ዜጎች በክለው ክብር የለሽ ሲያደርጉት በጣት የሚቆጠሩ ወራት እንኳ አልፈጀባቸውም፡፡ ‹‹አዲስ ንጉስ አንጂ ለውጥ መቼ መጣ!›› እንዲል ከያኒው፤ ካስወገዱት የደርግ መንግስት ጋር ልዩነታቸው-ደርጉ ያልቻለበትን የተቃውሞ ድምፆች በአዋጅ እንዲንቀሳቀሱ በአንድ በኩል ፈቅደው፣ በሌላ በኩል መልሶ ለመጨፍለቅ የፍርድ ቤቶችን ባረኮት የመጠቀም ባለ ሁለት ገፅ ብልጠታቸው ብቻ ነው፡፡
ይህ አይነቱ አገዛዝም ሥልጣን በያዘ ማግስት ሀገሪቱን እንዳሻው ለመርገጥ ሲቪል ቢሮክራሲውን ብቻ ሳይሆን የፍትሕ ስርዓቱንም በአምሳሉ አፍርሶ መስራት ነበረበት፡፡ ይሁንና ተቋሙን በዚህ መልኩ ለማዋቀር ጊዜ እንደሚያስፈልግ በመረዳቱ አሁን ድረስ በቂ መከራከሪያ ሊቀርብላቸው የማይችሉ ጉዳዮችን ከፍትሕ ሥርዓቱ ነጥቆ ሕገ-መንግስቱ ውስጥ በመዶል ለሌሎች ሰጥቷል፡፡ ለዚህ ደግሞ በቂ ማሳያ የሚሆነው፤ ሕገ-መንግስታዊነትን አስመልክቶ የሚነሱ የማጣራት ኃላፊነቶችን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት መስጠቱ ነው፡፡ በርግጥ አንዳንድ የወቅቱ ዘገባዎች እንደሚያሳዩት ሕገ-መንግስቱ በተረቀቀበት ሰሞን፣ ከሕገ-መንግስቱ የሚጣረሱ አዋጆች፣ ክሶች አሊያም ኩነቶች ሲፈጠሩ፣ የማጣራቱ ኃላፊነት የፍርድ ቤት መሆን አለበት ሲሉ የተከራከሩ ድምፆች ነበሩ፡፡ ዳሩ ውሎ-አድሮ ምን እንደሚሰሩ አስቀደመው የሚያውቁት ታጋዮች፣ በዛ ካድሬ-ዳኞች ባላፈሩበት ወቅት እንዳሻቸው ሕገ-መንግስቱን እየናዱ ቢያስሩ፣ አዋጅ ቢያወጡና ቢያስፈርዱ ድጋፉን የሚሰጣቸው ተቋም፣ በኢሠፓውያን እንደተሞላ የሚጠረጥሩት ፍርድ ቤት ሳይሆን፣ እንደ ልብ ሊቆጣጠሩት የሚችሉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት መሆኑን በመረዳታቸው፣ በፓርላሜንታዊ ሥርዓት ትመራለች በተባለች ሀገር ብዙም ባልተለመደ አኳኋን ሕገ-መንግስታዊ ትርጉም የሚሻቸውን ጉዳዮች የማጣራት ስራን ለዚሁ ምክር ቤት ሰጡት፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎንም በጥቂት ዓመታት ውስጥ የፍትሕ ተቋሙን በፓርቲ ፖለቲካ የተተበተበ፣ ለጉልበተኛ የሚገብር፣ ገንዘብ ሊገዛው የሚችል፣ ተቀናቃኝ ድምፆችን የማፈኛ መሳሪያ… አድርጎ የመቅረፅ ዓላማቸውን ማሳካት ችለዋል፡፡ በውጤቱም ተቋሙ የህግ የበላይነት የተደፈጠጠበት አድሎአዊና በየጊዜው ደካሞችን የሚያጠቃ ከሆነ እነሆ ከሁለት አስርት በላይ አስቆጥሯል፡፡
የሆነው ሆኖ የሥርዓቱን ፍትሕ ረጋጭነት በተጨባጭ ፍፃሜዎች አስደግፎ ለማቅረብ ሁለት አብነቶችን እጠቅሳለሁ፡፡ ቀዳሚው የበርካታ ግፉአንን እሪታ ሲወክል፤ ተከታዩ ደግሞ የገዥዎቹን የሙስና እና የጓዳ ፖለቲካ ትስስሮች ይጠቁመናል ብዬ አምናለሁ፡፡
የሞገስ ወልዱ-ጩኸት
ሰማይ ከመፍገጓ በፊት፣ ሁሌ ንጋት ላይ ኮተቤ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ተነስቶ፣ በእግሩ ሰከም ሰከም እያለ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ግድም ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይደርስና ዋናው በር ፊት ለፊት ቆሞ ከአንድ ሰዓት ላላነሰ ጊዜ ‹‹ሌባ ዳኛ!›› እያለ ይጮኻል፡፡ ያፏጫል፡፡ ‹‹እናንተ ገላችሁኛል፤ ቀብራችሁኛል፤ አምላክ ፍርዱን ይሰጣል!›› በማለትም ተስፋው በሰማያዊው መንግስት ላይ ብቻ እንደሆነ ያውጃል፡፡ …ይህ ሰው እንደምን ያለ ከባድ በደል ቢደርስበት ይሆን ምሬቱ እንዲህ ጣራ የነካው?
አሳዛኙ የሞገስ ታሪክ እንዲህ ይጀምራል፡- በ1997 ዓ.ም የወላጅ እናቱን ወ/ሮ አስካለ ቢፋ ህልፈት ተከትሎ፣ ወንድሙ ኃይሉ ወልደአማኑኤል የወራሽነት ድርሻውን እንዲያካፍለው ክስ መስርቶ ሲያበቃ፤ ሶስት ጥያቄዎችን ለፍርድ ቤቱ ያቀርባል፡-‹‹ንብረትነቱ የእናታችን የሆነ ቀበሌ 14/15 ውስጥ የሚገኝ 250 ካሬ ሜ. ላይ ያረፈ መኖሪያ ቤት፣ ሁለት ማሳ የእርሻ መሬት እና በንግድ ባንክ አራት ኪሎ ስላሴና መገናኛ ቅርንጫፍ የተቀመጠ መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብን ያካፍለኝ፡፡››
የከሳሽ ወንድም የሆነው ኃይሉም ፍርድ ቤት ቀርቦ ‹‹ቤትም ሆነ የእርሻ መሬት የሚባል ነገር የለም፤ በባንክ አለ ስለሚባለው ገንዘብም አላውቅም፤ እናታችን በሞተችበት ወቅት ስሟን ለማስጠራት ስል የእርሷ የነበረውን መሬት በ30 ሺህ ብር ሸጬ፤ ለአርባ፣ ለመንፈቅ፣ ለተስካር 10 ሺህ ብር ያወጣሁ ሲሆን፤ ቀሪውን 20 ሺህ ደግሞ ለወንድሜ ማረፊያ የሚሆን ቤት ሰርቼበታለሁ›› ሲል ምላሽ ይሰጣል፡፡ ችሎቱም ‹ቤቱንና የእርሻ መሬቱን በተመለከተ የቀረበ ማስረጃ አለመኖሩን› ገልፆ ‹የ30 ሺህው ጉዳይ ግን ያለይግባኝ ባይ ፍቃድ ወጪ የተደረገ ስለሆነ፤ የገንዘቡ ግማሽ 15 ሺህ ብር ድርሻው ስለሆነ እንዲሰጠው› በማለት ወስኖ መዝገቡን ይዘጋል፡፡ በውሳኔው እጅግ በጣም የተበሳጨው ሞገስ፣ ጉዳዩን በይግባኝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ይወስደዋል፤ ይግባኝ ሰሚውም ‹‹ቤቱ ይገኝበታል›› የተባለው ቀበሌ የእናታቸውን ማህደር እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ ግና፣ ሀገሪቷ ኢትዮጵያ ናትና፤ ቀበሌው ማህደሩ መጥፋቱን፣ ሟችም በተከሳሽ ቤት ይኖሩ እንደነበረ በደብዳቤ ያሳውቃል፡፡ ሆኖም ቀበሌው ይህንን ምላሽ ከሰጠ ከ14 ቀን በኋላ ‹የቀድሞውን አስተዳደር ጠይቄ ያገኘሁት መረጃ ነው› በማለት ለፍርድ ቤቱ እንዲህ የሚል ሌላ ደብዳቤ ይልካል፡- ‹ወ/ሮ አስካለ የግል መኖሪያ ቤት የነበራቸው ሲሆን፣ ቤቱ ያረፈበት መሬት ለ‹‹ሪል እስቴት›› በመሰጠቱ፤ ምትክ ቦታና ስድስት ሺህ ብር ወስደዋል›፡፡
የሰው ምስክሮችም ቀርበው ሟች እናት ቤት ሰርተው እንደነበረ ያረጋግጣሉ፡፡ ይህም ሆኖ የወ/ሮ አስካለ ማህደር ከቀበሌው ‹‹ጠፍቷል›› በመባሉ ምንም አይነት ማስረጃ ስላልቀረበ የቀድሞው ውሳኔ በይግባኝ ሰሚው ችሎትም ሊለወጥ አልቻለም፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮም ላለፉት ሁለት ዓመታት ከፍተኛው ፍርድ ቤት በር ላይ ቆሞ መጮኽን ስራዬ ብሎ ይዞታል፡፡ በርግጥ ከቀን ቀን አካላዊ መዳከም እየበረታበት መሄዱ በግልፅ ቢታይም የ40 ዓመቱ ጎልማሳ ሞገስ ወልዱ ዛሬም ከፍርድ ቤት ደጅ ቆሞ መጮኹና ማፏጨቱ የበርካታ ግፉአንን ድምፅ የሚወክል ይመስለኛል፡፡
ይህ ጉዳይ የሚያሳየው፣ የመንግስት ደመወዝ እየተከፈላቸው በዜጎች ሕይወት ላይ ሊወስን የሚችል እንዲህ አይነቱን ማስረጃ ያለአንዳች ጭንቀት ‹‹ጠፋ›› ብሎ ለመናገር የሚደፍሩ፣ ስለሕዝብ ብሶትና ችግር ምንም ግድ የሌላቸው ካድሬዎች እየተበራከቱ መምጣታቸውን ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም እንደ ሞገስ ያሉ የፍትሕ እጦት ረመጥ ሆኖ ያንገበገባቸው ምስኪኖች በአደባባይ ሲጮኹ ውለው፤ ሲጮኹ ቢያድሩ ‹‹ምን ይሆን ችግራቸው?›› ብሎ ለማድመጥ የሚሞክር አንድ እንኳን ባለሥልጣን መታጣቱንም ጭምር ነው፡፡
‹‹ሳይሰሙ ቀርተው ይሆናል!›› ማለቱን ከባድ የሚያደርገው ደግሞ፣ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አካባቢ የሚተላለፉ መንገደኞችም ሆኑ ወደ ተቋሙ የሚመጡ ባለጉዳዮች ክስተቱን የማወቃቸው እውነታ ነው፡፡ ከፖለቲካ ጋር በተያያዘ ፍርድ ቤት የሚቀርቡ ሰዎችን የችሎት ውሎ ለመሰለል ከተከሳሾች ቀድመው የሚደርሱ የደህንነት ሰራተኞችም ሞገስን ለማወቃቸው እኔው ራሴ ምስክር ነኝ፡፡
በአናቱም ከዚህ ቀደም በሸገር ራዲዮ ‹‹ኧረ በሕግ›› የሚል ፕሮግራም ያዘጋጅ የነበረውና በአሁኑ ወቅት በ97.1 ኤፍ.ኤም ‹‹የእኔ መንገድ›› የተሰኘ በተመሳሳይ ጭብጥ ዙሪያ የሚያተኩር ፕሮግራም የሚያዘጋጀው በሳሉ የሕግ ባለሙያ ሰለሞን ጓንጉል፣ ይህንን ታሪክ ከአንዴም ሁለቴ ለአድማጭ አድርሶታል፡፡ እንግዲህ እነዚህ ሁሉ ተደማምረው ነው ከቀበሌ አንስቶ ላይ ድረስ ያሉ መንግስታዊ መዋቅሮችን የዘረጋውና የሚቆጣጠረው የኢህአዴግ አመራር አባላት፣ የሞገስን ጩኸት ‹‹አልሰሙም›› ማለቱን ከባድ ያደረገው (በነገራችን ላይ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ግቢ ለአስር አመት ያህል በየቀኑ እየተመላለሱ የሚቆሙ አንዲት አዛውንት እና በፍትሕ ሚኒስቴር በር ላይ ቆማ መዋል ከጀመረች ስድስት ዓመት ያለፋት ራሄል የተባለች አቤት ባይ እንስት… መኖራቸውን አልዘነጋሁም)
ሙስና እና የጓዳ ፖለቲካ ትስስሮሽ
አገሪቷ በዚህ ሁሉ መፍትሔ እጦትና በፍትሕ መዛባት እየተመሰቃቀለችና በሕዝቦቿም ዋይታ እየተናወፀች ቢሆንም፤ መጽሐፉ ‹‹ዓይን አላቸው አያዩም፤ ጆሮ አላቸው አይሰሙም›› እንዲል፤ ገዥዎቻችን ይህን መሰሉን የድሆችና የአቅመ ደካሞች ብሶት መስማትን ፍፁም አይሹም፡፡ እነርሱ የታጋሉትም ሆነ የሚሰሙት አለቆቻቸውንና ባለፀጋዎችን ብቻ እንደሆነ ከሚያሳዩን በርካታ ማስረጃዎች መሃል ለአብነት አንድ ምሳሌ ላቅርብ፡-
ጉዳዩ በሙስና ተጠርጥሮ በእስር ላይ ከሚገኘው የቀድሞ ገቢዎችና ጉምሩክ ዳይሬክተር መላኩ ፈንቴ ጋር ይያያዛል፡፡ ከዚህ ሰው ሃያ አንድ ገፅ ከፈጀ የእምነት ክህደት ቃል ውስጥ ኮነ ምህረቱ የተባለ ግለሰብ በአራጣ ማበደር ተጠርጥሮ ከተያዘ በኋላ ‹‹እነአየለ ደበላ ለዳኛ ጉቦ ሰጥተው በዋስ ከእስር ተፈትተው፣ ከሀገር ለመውጣት ያስባሉ›› የሚል ‹‹መረጃ›› በመስጠት መተባበሩን ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስ እንደነገረው ገልፆ፣ ከእስር እንዲለቀቅ መደረጉን እናገኛለን፡፡ መቼም በሙስና ወንጀል ከተጠያቂነት የሚድን ተከሳሽ የሚሰጠው መረጃ ተጠርጣሪዎችን በሕግ ለመጠየቅ የሚጠቅም ሲሆን እንጂ፤ እንዲህ ባለ ከዋናው ክስ ጋር በማይዛመድ ተራና የአሉ-ባልታ ወሬ አለመሆኑን እነገብረዋህድና እነመላኩ ቀርቶ ማንኛውም መንገደኛ እንኳ ሊጠፋው አይችልም፡፡ አውቆ የተኛ… እንደሚባለው ካልሆነ በቀር፡፡
የሆነው ሆኖ ከመላኩ ፈንቴ የእምነት-ክህደት ቃል ትኩረት የሚስበው፣ ግለሰቡ በዚህ መልኩ ከሱ ተነስቶለት ከእስር ከተፈታ በኋላ ንብረቱና የባንክ ሒሳቡ መታገዱን አስመልክቶ የተፈጠረው ኩነት ነው፡፡ አቶ መላኩ ጉዳዩን ለመርማሪዎቹ ሲያብራራ ቃል-በቃል እንዲህ ነበር ያለው፡-
‹‹አቶ አባይ ፀሀዬ እና አቶ ደመቀ መኮንን ደውለው ‹ግለሰቡ አቤቱታ እያቀረበ ነው፡፡ ለምን አታዳምጡትም? ሲሉኝ፤ እኔም ከዚህ በኋላ ነው ግለሰቡን እቢሮዬ አግኝቼ ከላይ በገለፅኩት ሁኔታ እንዲስተናገድ ያደረኩት፡፡
እነዚህ ሰዎች ‹‹ነፃ አወጣነው›› የሚሉትን ሕዝብ ለስቃይ ዳርገው፣ ጥቂት ባለፀጎችን ብቻ ለማገልገል የቆሙ መሆናቸውን ለማስረገጥ ከዚሁ የእምነት-ክህደት ቃል አንድ ማሳያ ልጨምር፡- ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ የተባለ የአዲስ ልብ ህክምና ክሊኒክ ባለቤት ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው የሕክምና መሳሪያዎች (የልብ ፒስ ሜከር ተብሎ ተጠቅሷል) በሕገ-ወጥ መንገድ ሲያስገባ በቦሌ ኤርፖርት ጉምሩክ ሠራተኞች እጅ ከፍንጅ ከተያዘ በኋላ መለቀቁን በተመለከተ የህወሓት ከፍተኛ አመራር አባል የሆነው ዶ/ር ቴዎድሮስ አድህኖም ስልክ ደውሎ ‹‹ክሱን ብታነሱላቸውና በአስተዳደራዊ መፍትሔ ብትሰጧቸው›› ብሎ ከመንገሩም በላይ የግለሰቡ ክስ እንዲቋረጥ የሚጠይቅ ደብዳቤ እንደፃፈላቸው መላኩ ፈንቴ ለመርማሪዎቹ መናገሩ በመዝገቡ ላይ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ይህንን ሁናቴም ከወቅቱ የፖለቲካ አሰላለፍ አኳያ ስንተነትነው አቶ መላኩ ‹ዶ/ር ቴዎድሮስን መስማት፤ ህወሓትን እንደመታዘዝ ነው› የሚል እምነት አድሮበት የተባለውን ፈፀመ ብለን ብንደመድም ተምኔታውያን አያሰኘንም፡፡
እነዚህ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ያውም ሀገር በሚጎዳ ወንጀል የተከሰሰ ተጠርጣሪን በተመለከተ ከሥልጣን ገደባቸው አልፈው ‹‹አድምጥ!›› እያሉ የማዘዛቸው ምስጢር ሥርዓቱ ለፍትሕ ያለውን ግድየለሽነት እና በዚህ ሥርዓት የሕግ የበላይነት ብሎ ነገር እንጦሮጦስ መውረዱን ፍንትው አድርጎ ያሳያል ብዬ አምናለሁ፡፡ በርግጥ ይህንን ጉዳይ ለጥጠን ከተመለከትነው ‹‹…ለምን አታዳምጡትም?›› የምትለዋን ቃል ሰምና ወርቅ የለበሰች ቅኔ አድርገን በመውሰድ ልንፈታት እንችላለን፤ በተለይም መላኩ ፈንቴ ከዚህች ጥያቄ መሰል ትዕዛዝ በኋላ ግለሰቡን ቢሮ ጠርቶ ማስተናገዱን ስናስተውል፡፡
ምንም እንኳን አባይ ፀሀዬ በጊዜው በጉዳዩ ላይ መላኩን ሊያዝበት የሚያስችል መንግስታዊ ሥልጣን /የዕዝ ተዋረድ/ ባይኖረውም፤ አንጋፋ የህወሓት አመራር አባልና የበለጠ የፖለቲካ ጉልበት ያለው መሆኑ፤ ደመቀ መኮንን ደግሞ በብአዴን በኩል የአለቃነቱ ነገር ሲታሰብ፣ አሁንም መላኩ ፈንቴ የተጠየቀውን ‹‹ጥያቄ›› ከማስተናገድ ውጪ ሌላ አማራጭ አይኖረውም ወደሚል ጠርዝ ይገፋናል፡፡ በርግጥ እውነታው ይህ ቢሆንም፣ መላኩ ዛሬም እስር ቤት ውስጥ ሆኖ የቀድሞ አለቆቹንም ሆነ ራሱን ተጠያቂ ለማድረግ አልደፈረም፡፡ በግልባጩ ለቀረቡበት ክሶች በሙሉ ተጠያቂው ገብረዋህድ እንደሆነ ከመናገሩም በላይ እንዲህ በማለት ወንጅሎታል፡-
‹‹የአያት ባለቤት በግብር ማጭበርበር ተከሶ በነበረበት ወቅት የተከሳሹ ቤተሰብ የሆነ ሰው እቢሮዬ መጥቶ ‹ገብረዋህድ ምንም ጥፋት ሳያጠፋ ነው የአያት አክሲዮን ማሕበር ባለቤትን ያሳሰረው፤ አሁንም አንድ ሚሊዮን ብር ካመጣችሁ ከእስር ይፈታል ብሎናል› የሚል ጥቆማ አመጣልኝ፡፡ …ገብረዋህድ እና ነጋ ገ/እግዚአብሔር (የነፃ ትሬዲንግ ባለቤት ነው) ጓደኛሞች ናቸው፡፡ ነጋ ዕቃ ሲያስመጣ አያስፈትሽም፤ የነጋም ጓደኞች እነ አልሳም፣ ጌት አስ የመሳሰሉት ድርጅቶች ዕቃ በቀላል ቀረጥና ታክስ እንዲሁም አልፎ አልፎ ሳይፈተሹ ያልፋሉ፤ …ባለቤቱ ሃይማኖትም፣ በነጋ ድርጅት ውስጥ ትሰራለች…››
መላኩ ፈንቴ ይህንን ጉዳይ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ መናገሩንና ጠቅላይ ሚኒስትሩም፣ ፀጋዬ በርሄን ‹‹ተከታተል›› ብሎት እንደነበረ ከአስረዳ በኋላ እንደሚከተለው ይቀጥላል፡-
‹‹ገብረዋህድ በኋላ እንደነገረኝ ባለቤቱን ከነጋ ድርጅት አስወጥቶ በአዜብ ትዕዛዝ መሰረት ኤፈርት ውስጥ ያስቀጠራት መሆኑን ገልፆልኝ ‹አንተም ላይ የሚወራው ስለምትታገል ነው ብላኛለች አዜብ› ሲለኝ እኔም ተከታትዬ ፀጋዬ በርሄ ከምን እንዳደረሱት አልጠየኩም፡፡ መጠየቅ ነበረብኝ፤ ጥፋት ነው፡፡ በአጠቃላይ ገብረዋህድ ላይ ብዙ ነገር ይባል ነበር፡፡››
መቼም ይህ ምላሽ በ1981 ዓ.ም ከአስመራ ዩንቨርስቲ በኢኮኖሚክስ ዲግሪውን፣ ከአውስትራሊያ በገቢ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪውን፤ ከለንደንም በቢዝነስ አስተዳደር በተመሳሳይ መልኩ ትምህርቱን ካጠናቀቀና የረዥም ዓመታት የስራና የፖለቲካ ተሞክሮ ካለው ሰው የተሰጠ መሆኑን ስናስተውል፤ ሀገሪቱ የአምባገነን ባለሥልጣናት መቀለጃ ብቻ ሳትሆን፤ የሰዎቹንም የአቅም ማነስ ያመላክታል፡፡ እንዲሁም እነሞገስ ሰሚ ያላገኙበትን ምክንያትም ሆነ በዚህች ሀገር ገንዘብ ያለው የፈቀደውን መፈፀም የመቻሉን ምስጢር ይገለፅልናል፡፡
ኢህአዴጋዊ ዕድሜ ማራዘሚያ…
ገዥው ስብስብ የፍትሕ ስርዓቱን ተቋማዊነት ሳይነካ፣ ለጨቋኝነቱ መጠቀሚያ የሚያደርግበት አንዱ መንገድ ከጠቅላይ እስከ ታች በተዋረድ የሚገኙ ፍርድ ቤቶች ድረስ ያሉ ዳኞችን የሚመድብበት አካሄድ ነው፡፡ በርግጥ እንዲህ አይነቱ ሀገርና ሕዝብ አልያም ሞራላዊ ልዕልና እና የሕግ-የበላይነት የማያስጨንቀው አገዛዝ፣ የፍትሕ ስርዓቱ ቅጥ የለሽ ተባባሪነት ሳይታከልበት የሥልጣን ዕድሜውን ማራዘም እንደማይችል መረዳት አይሳነውም፡፡ ይህን ለማድረግም ያለው ብቸኛ ምርጫ ዳኞቹን ከስሩ መሰብሰብ ይሆናል፡፡ ለዚህ ደግሞ ኢህአዴግ መሩ-መንግስት ሁለት አካሄዶችን ለመተግበሩ ያሳለፋቸው ሁለት አስርታት በሚገባ ያሳያሉ፡፡
የመጀመሪያው የሚሾሙት ዳኞች፣ የግንባሩ ከፍተኛ የካድሬ ማሰልጠኛ እንደሆነ ከሚነገርለት ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ ተማሪዎች መካከል ማድረጉ ነው፡፡ ከዚህ ‹‹የትምህርት›› ተቋም ውስጥ የሚወጡ የሕግ ምሩቃን ደግሞ ስለጥልቅ ዘመናዊ የሕግ ፅንሰ-ሃሳብ ለማወቅ ከመትጋት ይልቅ፤ የኢህአዴግ ፖሊሲዎች እና አብዮታዊ ዲሞክራሲ ሕግን እንዴት ‹‹ለመደብ ጠላት›› መጠቀም እንደሚያስችሉ በሚሰብኩ መምህራን ስር እንዲያልፉ ይገደዳሉ (ስለመምህሮቹ ምሁራዊ ልሽቀት ለመረዳት የሕዝብ ሙስሊሙን ጥያቄ በሽብር ተግባር ለመፈረጅ እና ማሕበረ ቅዱሳንን በአክራሪነት ለመወንጀል በ‹‹ጥናታዊ ጽሑፍ›› ስም የተጓዙበትን ርቀት ማየቱ ብቻ በቂ ይመስለኛል)፡፡ ተማሪዎቹም በዚህን መሰሉ የካድሬ ተቋም ስልጠና ስር ሰንብተው ሲወጡ፤ በፍፅምና ሊታመኑላቸው ይገቡ የነበሩትን ፍትሓዊ ዳኝነትና ህሊና የሚባሉ ጉዳዮችን ጨፍልቀው፣ በተለይም ፖለቲካዊ ነክ በሆኑ አይረቤ ክሶች ፊታቸው በሚቆሙ ንፁሀን ዜጎች ላይ መከራን የሚያዘንቡ አሽከሮች ይሆናሉ፡፡ ይህንን አስነዋሪነት ካለመታከት የሚፈፅሙትም፣ ሥልጣንን እና ተያያዥ ጥቅማ-ጥቅሞችን እያጋበሱ ወደ ከፍታ ሲወጡ ተመልክተናል፡፡
ሁለተኛው የግንባሩ አካሄድ ከካድሬ ማሰልጠኛውም ሆነ የተሻለ ነው ከሚባለው የአ.አ.ዩ. የሕግ ፋካሊቲ የሚመረቁትን፣ በተከታታይ ርዕዮተ-ዓለማዊ ጠመቃ የሥርዓቱ ጋሻ-ጃግሬ ማድረግ ላይ ያተኮረው ነው፡፡ በሀገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ሲያገለግሉ ቆይተው ስደትን የመረጡ ዳኞችና ዐቃቢ-ህግያት በተለያየ ጊዜ እንደ መሰከሩትም አሰልቺ የርዕዮተ-ዓለም ጠመቃ የፍትሕ ሥርዓቱን ነፃነት ጽልመት ካላበሱት ሂደቶች በዋነኛነት ተጠቃሽ ነው፡፡ በአንድ ወቅትም ሟቹ አቶ መለስ ዜናዊ የሀገሪቱን ዳኞች ሰብስቦ ስለሕገ-መንግስት እና ሕገ አተረጓጎም መርህ ሲያስተምር ለማየት የተገደድነው የዚሁ የጠመቃው አንድ አካል በመሆኑ ይመስለኛል፡፡ ዳሩስ፣ ይህማ ባይሆን ኖሮ እስክንድር ነጋ ላይ 18 ዓመት መፍረድ ሕሊና እንዴት ይፈቅድ ነበር? ኦልባና ሌሊሳንስ ለ11 ዓመታት ወህኒ ያስወረወረው ጥፋት ምን ተብሎ በአሳማኝ መልኩ ሊጠቀስ ይችል ይሆን?

ESAT Yederegetse Dassesa April 11,2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Yederegetse Dassesa April 11,2014 Ethiopia | ESAT Tube

Thursday, 10 April 2014

ESAT Daily News Amsterdam Apr 10 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Daily News Amsterdam Apr 10 2014 Ethiopia | ESAT Tube

ESAT Menalesh Meti with Norwegian Activists April 2014 | ESAT Tube

ESAT Menalesh Meti with Norwegian Activists April 2014 | ESAT Tube

“ንብረት የማፍራት መብት መገለፅ ያለበት በብሔረሰብ ደረጃ ሳይሆን በግለሰብ ነው” – አቶ ተክሌ በቀለ (የአንድነት ፓርቲ ም/ፕሬዝዳንት) – በዘሪሁን ሙሉጌታ

April 10th, 2014
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሁለተኛውን የሕዝብ ንቅናቄ መጀመሩ የሚታወስ ነው። ፓርቲው ከዚህ ቀደመ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል የሕዝባዊ ንቅናቄ መድረኮች አዘጋጅቷል። አሁን ደግሞ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪ ቃል ፕሮግራሙን ይፋ አድርጓል። ባለፈው እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም በደሴ ከተማ ፕሮግራሙን በሰላማዊ ሰልፍ አከናውኗል።
በደሴ ስለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍና “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚለው ርዕሰ ጉዳይ ላይ የፓርቲውን ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለ፣ የፓርቲው የውጪ ግንኙነት ኃላፊ ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ እና የፖርቲው ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ሰልፉን መርተውታል። ከመሬት ባለቤትነትና ከሰልፉ ጋር በተያያዘ የፓርቲውን ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለን አነጋግረናቸዋል።
ሰንደቅ፡- በደሴ ያካሄዳችሁት ሰላማዊ ሰልፍ ምን ያህል የተሳካ ነበር?
አቶ ተክሌ፡- መጀመሪያ ፕሮግራሙን ያሰብነው በሐዋሳ፣ በአዲስ አበባና በደሴ ከተሞች ነበር። እንደአጋጣሚ ሆኖ የደሴው በመሳካቱ ቅስቀሳ ስናደርግ ቆይተን ሰልፉን ለማካሄድ በቅተናል። የአዲስ አበባውና የሐዋሳው ለሌላ ጊዜ ተዛውሯል። የሐዋሳውን በራሳችን ምክንያት ያራዘምነው ሲሆን፤ የአዲስ አበባው ግን በአስተዳደሩ ችግር ምክንያት ነው።
የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ እንደጠበቅነው በከፍተኛ ሞቅታ ነው ፕሮግራሙ የተጀመረው። በርካታ ሕዝብ ተገኝቶልናል። የሰልፉ አካል ሆኖ በመሐል መንገድ ላይ መፈክር እያሰማ ሲሄድ የነበረው የሕዝብ ብዛት ከ50 እስከ 60 ሺህ ገምተነዋል። ከሰልፉ ጎን ለጎን ዳርና ዳር የሚሄደው ሕዝብ በግምት መቶሺህ ይሆናል። በእኛ እምነት ሕዝቡ በመሬት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የመሬት ጉዳይ የሚያስከፍላቸውን ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመገንዘብ ከፍተኛ የሆነ መነሳሳት አሳይቷል። በተደረገው የሁለት ቀን ቅስቀሳ ያን ያክል ሕዝብ መውጣቱ የሕዝቡም ስሜት ከፍተኛ እንደነበር ያሳያል። በዚህ ወቅት እኔን ያስታወሰኝ በ2002ቱ መርጫ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ “ደሴም ሳይቀር አሸንፈናል” ብለው ነበር። አሁን ሳየው ግን የኢህአዴግ የምርጫ ኮንትራት ሳያበቃ ይሄን ያክል ሕዝብ ወጥቶ “በቃኝ” የማለቱ ሁኔታ ሲታየ ምርጫውን እንዴት ነበር ያሸነፉት ብዬ እንዳስብ አድርጎኛል።
ሰንደቅ፡- መሬት የፖሊሲ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን ከሰላማዊ ሰልፍ ይልቅ በሕዝባዊ ውይይት ማካሄዱ ይሻላል፤ አለበለዚያ በትንሹም በትልቁም ሰላማዊ ሰልፍ መጥራት የፓርቲውን ደጋፊዎች ያሰለቻል የሚል ነገር እየተነሳ ነው። ለዚህ ኀሳብ ያለዎት ምላሽ ምንድነው?
አቶ ተክሌ፡-ፕሮግራሙ ሲጀመር የመረጥናቸው ከተሞች ነበሩ። አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ የሀገሪቱ ምሁራን የሚገኙበት የአዳራሽ ውስጥ ስብሰባ አቅደን ነበር። ወደ አደባባይ እየገፋን ያለው ኢህአዴግ ነው። መሬትና ከመሬት ጋር ተያይዞ ለሚፈጠሩ ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊና የፍትህ ችግሮች በተመለከተ በሰላማዊ ሰልፍና በሕዝባዊ የአዳራሽ ስብሰባ ለይተን ነበር። ነገር ግን ገና ከመጀመሪያው አዲስ አበባ ላይ አዳራሽ ማግኘት ተቸግረናል። የመንግስት አዳራሾች ብቻም ሳይሆን በገንዘባችን ከፍለን የሆቴሎችን አዳራሽ ማግኘት አልቻልንም። ወደ ጎዳና እየገፋን ያለው ገዢው መደብ ነው።
ሰንደቅ፡- የመሬት ችግር በከተማና በገጠርም የተለያየ ነው። በሀገሪቱም የችግሩ አይነትና መጠንም የተለያየ ነው። በቀላሉ የሕዝብ ድጋፍ አላችሁ ተብሎ በሚገመተው ደሴ ከተማ ከማካሄድ ይልቅ በደቡብና ኦሮምያ ክልሎች ለምን እንቅስቃሴውን አልጀመራችሁም?
አቶ ተክሌ፡- በአጠቃላይ በመሬት ላይ ያለን እይታ ሦስት አይነት ነው። መሬት በግል፣ በወል ወይም በመንግስት ስር መሆን አለበት የሚል የመሬት ስሪት አቋም አለን። ኢህአዴግ ደግሞ መሬትን በተመለከተ የሚያስቀምጠው ከእኛ ፍፁም የተለየ ነው። በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40 ንዑስ ቁጥር ስድስት ላይ መሬት የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንደሆነ አድርጎ ነው የሚያስቀምጠው። ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በባህል፣ ወዘተ እንጂ ንብረት በማፍራት መብታቸው ሊገለፅ አይችልም። ንብረት የማፍራት መሠረታዊ መብት መገለፅ ያለበት በብሔረሰብ ደረጃ ሳይሆን በግለሰብ ነው። ኢህአዴግ ብሔር ብሔረሰቦች የሚያቋቁሙት መንግስት ነው ብሎ ስለሚያምን በተዘዋዋሪ መሬት የመንግስት እንደሆነ መረዳት ይቻላል። ይህ ማለት ደግሞ በብሔር ብሔረሰቦች ስም መሬትን ወይም የሕዝብን ንብረት ጠቅልሎ ኢህአዴግ ወስዶታል ማለት እንችላለን። በሌላ አነጋገር ግለሰቦች ከመሬት ባለቤትነት ውጪ ሆነዋል ማለት ነው። በእኛ እምነት የከተማ መሬት የግለሰቦች መሆን አለበት ብለን እናምናለን። የገጠሩ ደግሞ አስቀድሜ እንደነገርኩህ በግል፣ በወል ወይም በጋራ እና በመንግስት መያዝ አለበት።
ወደ ጥያቄህ ስመጣ አጠቃላይ የኢህአዴግ የመሬት ፖሊሲ በብሔር ብሔረሰቦች ሽፋን ከመውሰዱ አንፃር ችግሩ የመላ ሀገሪቱ ነው። ስለዚህ በደሴም ጀመርከው በደቡብ ችግሩ አንድና ተመሳሳይ ነው። በእርግጥ በደሴ የጀመርነው የተሻለ ተቀባይነት አለን በሚል መነሻ ብቻ አይደለም። አንድነት አጠቃላይ ሕዝቡ ከተቃዋሚው ጎራ ጋር እንደወገነ እንረዳለን። ኢህአዴግ የሚዘጋብን ሕዝቡ እንደሚደግፈን ስለሚያውቅ ነው። በእርግጥ አንድነት ያልደረሰባቸው፣ ሌሎች ተቃዋሚዎች ጠንካራ ስራ የሚሰሩባቸው ቦታዎች ይኖራሉ። ያም ሆኖ ስንጀምረው አዲስ አበባና ሐዋሳ ነበር። ደሴ አልነበረም።
ሰንደቅ፡- ገዢው ፓርቲ ተቃዋሚዎች በመሬትም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ላይ የጠራ ፖሊሲ የላቸውም እያለ ነው። በእናንተ እምነት በአሁኑ ወቅት የጠራ ፖሊሲ አለን ብላችሁ ታስባላችሁ?
አቶ ተክሌ፡- በመሬት ላይ ብቻ አይደለም። በአጠቃላይ ከመሬት ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች በርካታ ናቸው። የሀገሪቱ አንጡራ ሀብት መሬት እንደሆነ አንረዳለን። ዋነኛ ትኩረታችንም የመሬት ምርታማነት፣ ባለቤትነትና ልማት ነው። ከገዢው ፓርቲ ጋር ካሉን የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብት የአከባበር ልዩነቶች ባሻገርም አንዱና ዋነኛው መሬት ነው። ከሀገሪቱ የችግር ምንጮች ውስጥ አንዱ የመሬት ባለቤትነት ነው። ስለዚህ በዚህ ዙርያ ያሉ ችግሮችን ተረድተናል። ችግሮቹን በመረዳታችንም የጠራ ፖሊሲ ቀርፀናል። ከመሬት ባሻገርም በፋይናንስም በለው፣ በግብርናም ሆነ በውጪ ጉዳይ በማኅበራዊ ጉዳዮች ሀገሪቷዋን ከድህነትና ኋላቀርነት ያወጣል ብለን እናምናለን። ችግራችን የቀረፅናቸውን አማራጭ ፖሊሲዎች ለሕዝብ ማድረስ የምንችልበት የሚዲያ እና ወደ ሕዝቡ የምንቀርብበት መድረክ መዘጋቱ ነው። እና ኢህአዴግ “ተቃዋሚዎች አማራጭ የላቸውም” የሚለው አባባል ድሮ የቀረ ተረት ተረት ነው።
ሰንደቅ፡- በተቃዋሚዎች በኩል ወጥ የሆነ የመሬት ፖሊሲ አይስተዋልም። በተለይ በኦሮሞ ብሔር የተደራጁ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መሬት የመንግስት ይሁን የሚል ዝንባሌ አላቸው። ሌሎቻችሁ ደግሞ “መሬት ይሸጥ ይለወጥ” እስከማለት ትደርሳላችሁ ይህ ደግሞ በምርጫ ወቅት አያስቸግርም?
አቶ ተክሌ፡- ተመሳሳይ ፕሮግራም ያላቸው ፓርቲዎች ውህደት ፈጥረው በአንድ ላይ ቢንቀሳቀሱ ችግሩ ሊፈታ ይችላል። የግል ስልጣንና የቡድናዊ ጥቅምን አስወግደው ወደ ውህደት ቢመጡ መልካም ነው። አሁን ፓርቲዎች ሚዛን በማይደፉ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ቢሆንም፤ ያነገቡት ፕሮግራም የተለያየ አይደለም፤ በመሆኑም ሕዝቡ የተለያዩ ፓርቲዎችን ቢመርጥም የሚመረጠው ፕሮግራም ግን ተቀራራቢና በአመዛኙ አንድ አይነት ነው ለማለት ያስደፍራል። በእርግጥ ከመድረክ ጋር በተያያዘ አንዱ ልዩነት የመሬት ባለቤትነት ጉዳይ ነው። ሆኖም ግን በመለስተኛ ፕሮግራማችን ላይ መሬትና ያልተፈቱ ሌሎች ጥያቄዎችን ሕዝቡ እንዲፈታቸው ተስማምተናል። ነገር ግን ሕዝቡ ደግሞ ደሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶቹን ሙሉ በሙሉ አልተጎናፀፈም። መሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ መብቶቹን ያልተጎናፀፈ፣ ሕዝብ ዋነኛ በሆኑ የሕዝብ ችግሮች ላይ መፍትሄ ለማምጣት መጀመሪያ የተነፈገውን መብት ማግኘት አለበት የሚል መረዳት አለ። በመሠረቱ የተጠቀሱት የኦሮሞ ድርጅቶችም መሬት የመንግስት ይሁን ሳይሆን፤ ሕዝቡ ይወስን እያሉ ነው። አረናን ብትወስደው መሬት የግል ቢሆንም፤ መሸጥ መለወጥ የለበትም ይል እና ጉዳዩ የሕገ-መንግስት ማሻሻያን የሚጠይቅ እንደመሆኑ ሕዝቡን ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው። በድምሩ ስታየው መሬትን በተመለከተ በተቃዋሚዎች ካምፕ ያለው መረዳት የሚያራራቅ ሳይሆን ሊታረቅ የሚችል ጉዳይ ነው።
ሰንደቅ፡- ፓርቲያችሁ በአሁኑ ወቅት የመሬትን ጉዳይ ያነሳው ለምንድን ነው?
አቶ ተክሌ፡- ኢትዮጵያ ውስጥ የስልጣን መባለግን ጨምሮ ከፍተኛ የሙስና ምንጭ የሆነው መሬት ነው። የመሬት ጉዳይ የፍትህ እጦትና የመልካም አስተዳደር ችግር መገለጫዎች አንዱና ዋነኛው ነው። ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ አዝጋሚነትና ለማኅበራዊ ችግሮች ምንጩ የመሬት ባለቤትነትና የይዞታ አስተዳደር ችግር ነው። ይህንን እኛ ብቻ ሳንሆን እራሱ ገዢው ፓርቲ የሚያምንበት ጉዳይ ነው። በዚህ ወቅትም ጉዳዩን ልናነሳው የቻልነው ከመሬት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮች ላይ ግንዛቤ ለመጨበጥ፣ ባለን ፖሊሲም ላይ እንደ ግብአት የሚያስፈልግ ነገር ካለም ለማካተት ነው። በዋናነት ግን የሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውሶች መገለጫ መሆኑን፣ የኢህአዴግ የመሬት ፖሊሲ የተሳሳተና ያስከተለውንም በሙስና የመጨማለቅ ሁኔታን ለማሳየት ነው።
በአሁኑ ወቅት መሬት በኢንቨስትመንት ስም የሙስና መንጭ ሆኗል። ግለሰብ በግለሰብነቱ ከመሬት ባለቤትነት ከራቀ በፖለቲካ ዓይን ስታየው የካድሬዎች መጫወቻ ይሆናል። ይህንን ማረጋገጥ የሚቻለው በተለያዩ ጊዜአት መንግስት የሚያስራቸው ባለስልጣናቱን እያየን ነው።
ሰንደቅ፡- በቀጣይ የምታካሂዱት እንቅስቃሴስ ምን ይመስላል?
አቶ ተክሌ፡- በትላልቅ ከተሞች በተለይም ምሁራንን በቀላሉ በምናገኝበት ቦታ የአዳራሽ ስብሰባዎች እያደረግን፣ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ይደረጋል። በገጠር ደግሞ በወረዳ ደረጃ የሚሰሩ ስራዎች አሉ። ሰላማዊ ሰልፎቹም በተመረጡ ከተሞች ይቀጥላሉ። እንደነገርኩህ መሬትን በተመለከተ ሕዝቡ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝ ዋነኛ ዓላማችን ነው። በገጠሩም በከተማም ሰፊ እንቅስቃሴ እናደርጋለን ብለን አቅደናል።
ሰንደቅ፡- ይህ መሬትን ማዕከል ያደረገ እንቅስቃሴ በቀጥታ ከ2007ቱ ምርጫ ጋር የሚያያይዘው ነገር አለ?
አቶ ተክሌ፡- ከምርጫ ጋር አይያያዝም። ምርጫ እንገባለን ወይስ አንገባም የሚለው የብሔራዊ ምክር ቤቱ ውሳኔ ነው የሚሆነው። በአጠቃላይ ያሉትን ሁኔታዎች እያየን የምንወስነው ጉዳይ ነው። አሁን ግን የመሬት ጉዳይ ያለንን ፖሊሲ ከማዳበርና ኅብረተሰቡም በመሬት ላይ የጠራ ግንዛቤ እንዲኖረው ማድረግ ነው።1497470_617770758307862_5102468884195852277_n

የአዲስ አበባ መስተዳድር የእውቅና ደብዳቤ ጻፈ ፓርቲው አልተስማማም::

April 10th, 2014
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለመጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ሊያደርገው ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የመስተዳድሩ የሰላማዊ ሰልፍና ማሳወቂያ ክፍል ዘግይቶ በጻፈው ደብዳቤ የሰልፉ ቀን በሌላ ፕሮግራም መያዙን በመጥቀስ የቀን ለውጥ እንዲደረግ መጠየቁ አይዘነጋም፡፡
ፓርቲው የቀረበውን አስተያየት በመቀበል ሰልፉ ለሚያዚያ 5 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ መወሰኑን በመግለጽ ለመስተዳድሩ አሳውቋል፡፡ሆኖም መስተዳድሩ ዕለቱ በታላቁ ሩጫ መያዙን በመጥቀስ ለፖሊስ ጥበቃ ለመስጠት የሚያስቸግረው በመሆኑ ሰልፉ ለሚያዚያ 4 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲደረግ የእውቅና ደብዳቤ ጽፏል፡፡ ፓርቲው በመስተዳድሩ የተሰጠውን እውቅና አለመቀበሉን ለማሳወቅ ከፍተኛ አመራሮቹን ወደ ከንቲባው ጽ/ቤት ልኮ የአንድነት አመራሮቹና የመስተዳድሩ ሰዎች በጉዳዩ ዙሪያ የተነጋገሩ ሲሆን ዝርዝሩን እንደደረስን አንገልጻልን፡፡10246341_617446441673627_5446260811692987854_n

የቶሮንቶና የነቀምት ግንባር፣ የአንድነት የሶስት ወር ዘመቻ

April 10, 2014
የማርቆስ ብዙነህ ደብዳቤ፤
1-     “በርካታ ትምህርት ቤቶች፤ ዩኒቨርስቲና የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ፤ የተጠየቀው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን” ይላል፤ በአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቅ ክፍል ሀላፊ፤ በአቶ ማርቆስ ብዙነህ ማንደፍሮ፤ መጋቢት 23 ቀን 2006/2014 የተፈረመው ደብዳቤ፡፡ አንድነት፤ ሰልፉን ለማድረግ ያቀረባቸው መስመሮች 3 ሲሆኑ፤ ሶስቱም መስመሮች ከቀበናው የአንድነት ጽ/ቤት ይነሳሉ፡፡ አንደኛው መስመር በአራት ኪሎና በፒያሳ አድርጎ፤ ወደ አዲስ አበባ መስተዳድር ጽ/ቤት ያመራል፡፡ ሁለተኛው አማራጭ በአራት ኪሎ ተጉዞ፤ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን አልፎ መስቀል አደባባይ ያበቃል፡፡ ሶስተኛው አማራጭ፤ በአራት ኪሎ ፒያሳ፤ ቸርችልን ይዞ ድል ሀውልት ጋር ያበቃል ነበር የሚለው፡፡ ከላይ እንደተመለከታችሁት፤ የአዲስ አበባ መስተዳድር፤ ሶስቱም አማራጮች አልተመቹትም፡፡ የተመረጡት መስመሮች በርካታ ትምህርት ቤቶች የትምህርትና የመንግስት ተቋማት ስለሚገኙበት፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ግንባታ ያለባቸው መንገዶች ስለሆኑ፤ እንዲሁም በእለቱ የህዳሴው ግድብ ግንባታን የተመለከቱ ዝግጅቶች ስላሉ፤ መስተዳድሩ ሰልፉን ሳይፈቀድ ቀረ፡፡
2-    አንድነት ክልከላው ሕገወጥ ነው፤ ሰልፋችንን እንቀጥልበታለን ብሎ አቋሙን ሲያሳውቅ፤ የአዲስ አበባ መስተዳድር ዘግይቶም ቢሆን፤ ተለዋጭ ቀንና መንገድ እንደሚቀበል ጠቆመ፡፡ ወትሮም ቢሆን የአዲስ አበባ መስተዳድር የተከተለው ስልት የማዳከም፤ የማበሳጨት፤ የማሰናከልና ተስፋ የማስቆረጥ እንጂ ጨርሶ የመከልከል አይመስልም፡፡ ስለዚህም ድርጅቱ በተዘጋጀበትና በመረጠው ቀን ባይሆንም፤ በሌላ ቀን እንዲሆን ለመለወጥ አስገደደ፡፡ በርግጥ የአዲስ አበባ መስተዳድር የመጀመሪያውን ሰልፍ ያሰናከለበት ምክንት አግባብ ባይሆንም፤ የአንድነት ልሳን ፍኖተ-ነጻነት፤ የአዲስ አበባ መስተዳርን የዘገየ እሺታ አስጩሆ የዘገበበት መንገድ ብልሀት ይጎድለዋል፡፡ ፍኖት ነጻነት፤ “በመጨረሻ የአዲስ አበባ መስተዳድር እጅ ሰጠ” ነው ያለው፡፡ ይሄ አይነቱ ረታናችሁ፤ አሸነፍናችሁ አካሄድ መንግስት የሚያሸሽ ስለሆነ፤ ፍኖተ ነጻነት ከዚህ አይነቱ አናዳጅ ርእሰ-ዜና መራቅ አለበት፡፡ ኢሳትም ይሄን አይነት ሰራንላችሁ፤ የታባታችሁ የሚል አዋራጅ አዘጋገብ አልፎ አልፎ ይተገብራል፡፡ ፈጣሪ ጊዜና ጉልበት ከሰጠኝ፤ ይሄ አይነቱ ጠላትን የማዋረድና የጽንፈኝነት አካሄድ ለምን እንደሚጎዳ እጽፋለሁ፡፡ ለጊዜው የፍኖተ ነጻነት ርእስ እንዳልተመቸኝ ሳልጠቅስ አላልፍም፡፡
ስለሕገመንግስት፤ መብት ተረጋግጧል ወይስ ተረግጧል
3-   የሆነ ሆኖ፤ ወደሰልፉ ጉዳይ ስንመለስ፤ አሁን በስራ ላይ ባለው የኢትዮጵያ ሕገመንግስት መሰረት፤ ዜጎች በመሰላቸው ርእስ፤ በጣማቸው ምክንያት፤ በታያቸው ሕልም፤ በተሰማቸው ደስታ፤ ባሳዘናቸው ሰበብ፤ መንግስትን ደግፈውም ይሁን ተቃውመው፤ ሀሳባቸውን በተቃውሞ ወይም በድጋፍ የመግለጽና የመሰብሰብ መብታቸው ተረጋግጧል፡፡ ሕገ-መንግስቱ ራሱን በራሱ ያስፈጽም ይመስል፤ ሕወሀት/ኢህአዴግ ብዙውን ግዜ እንዲህ ያለው መብት በሕገ መንግስቱ ተከብሯል፤ በሕገመንግስቱ ተረጋግጧል እያለ የሚያጭበረብረው ነገር ስላለ፤ ይሄንን የተቃውሞ ሰልፍ በህገመንግስቱ ተከብሯል የሚል አረፍተነገር የተመለከተ ሰው፤ ጥንቃቄ ካላደረገ በስተቀር በሀይለኛው ይሳሳታል፡፡ በሕገ መንግስቱ መሰረት፤ ተረጋግጧል የሚለው ቃል፤ ተከብሯል በሚለው መተርጎም ቢኖርበትም፤ በኢትዮጵያ በተግባር እንደምናየው ግን፤ ተከብሯል በሚለው ሳይሆን፤ በሕገመንግስት ተረግጧል በሚለው ቢተረጎም ይቀላል፡፡ መብቱ በሰበብ አስባቡ ተሸራርፏል፡፡ በአንድነትና በሰማያዊ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ላይ የሚደርሰውን ለተመለከተ ይሄንን መረዳት አያዳግተውም፡፡
4-   ለምሳሌ ሕገመንግስቱ ሰልፍ ከማድረግ በፊት ለሚመለከታቸው አካላት ስለማሳወቅ ብቻ ሲናገር (የአቶ ማርቆስ ብዙነህ ማህተም የሰልፍና ስብሰባ ማሳወቅ ኦፊሰር ነው ይላል)፤ ህግ አውጪዎቹና አስፈጻሚዎቹ ደግሞ፤ የለም ሰልፍ አሳውቅ ሳይሆን አስፈቅድ ነው ብለው ተረጎሙት፡፡ መተርጎም ብቻ ሳይሆን፤ ሕገ መንግስቱ ያረጋገጠውን መብት፤ ሰልፍን የተመለከቱ አዋጆችና ደንቦች አውጥተው ረጋገጡት፡፡ ለምሳሌ የአዲስ አበባ መስተዳድር የስብሰባና ሰልፍ አሰራር ስነ-ስርአት አንቀጽ 5.1 ከላይ በተጠቀሱት የመንግስትና የትምህርት ተቋማት አካባቢ ሰልፍ ማድረግ አይቻልም ይላል፡፡ በካናዳ ቢሆን፤ እነዚህን ሕገመንግስታዊ መብት የሚሸራርፉ አዋጆችና ደንቦች፤ ፍርድቤቶች ዋጋ የለሽ ህጎች ብለው ይወስኑባቸው ወይም ያመክኗቸው ነበር፡፡ እኛ አልታደልንምና፤ እስካሁን እንዳየነው፤ የኢትዮጵያ ፍርድቤቶች እንዲህ ያለውን ሕግ የመሻር ወይም፤ ሕገመንግስቱን ይጥሳል ብለው የመወሰን ስልጣንም ወኔውም አልተመለከትንባቸውም፡፡ ከተመለከትንም፤ ወይ ፍርዱ ወይ ዳኛው አይጸናም፡፡ መንግስት እንዲህ ነው ካለ፤ የኢትዮጵያ ፍርድቤቶችም አብረው እንዲያ ነው ይላሉ፡፡ ከመንግስት ጋር ይስማማሉ፡፡
የት ሄደን እንሰለፍ፤ ነው ወይስ እንሰየፍ
5-   ሰልፍ 48 ሰዓት ቀደም ብለህ አሳውቅ የሚለው ድንጋገጌ ሰልፍ አስፈቅድ በሚለው አዋጅ ተሸርፎ ብቻ አላቆመም፡፡ ከአንድነትና መኢአድ እንዲሁም ሰማያዊ ፓርቲ ስኬታማ ሰልፎች በኋላ ደግሞ ሰሞኑን የምንመለከተው፤ ጭራሽኑ ሰልፍ መሰለፊያ ስፍራ የሚያሳጣ ሁኔታ እንዳለ ነው፡፡ ቀደም ሲል ሰልፍ የተከለከለባቸው ስፍራዎች የጦር ሰራዊት ካምፖች፤ ሆስፒታሎችና መሰል ስፍራዎች ነበሩ፡፡ ከሰሞኑ ደግሞ በትምህርትቤቶች ወይም ዩኒቨርስቲዎች አካባቢም ሰልፍ ማድረግ አይቻልም የሚል ደንብ ወጣ፡፡ ቀጥሎ በእምነት ተቋማት ማለትም በመስጊድና በአብያተክርስቲያናት አካባቢ አይቻልም የሚል አዋጅ/ደንብ ይመጣል፡፡ በአዲስ አበባ በሁሉም ማእዘን ቢኬድ፤ ትምህርትቤት ባይኖር፤ ሆስፒታል አለ፤ ሆስፒታል ባይኖር፤ የጦር ካምፕ አለ፤ የጦር ካምፕ ባይኖር፤ ቤተ-እምነት አለ፤ ቤተ-እምነት ባይኖር፤ ዩኒቨርስቲ አለ፤ ዩኒቨርስቲ ባይኖር መዋእለ-ሕጻናት አለ፤ ያም ባይኖር የሆነ ነገር አለ፡፡ ስለዚህ አዲስ አበባ ውስጥ ሰለፍ ሊደረግ የሚችልባቸው ስፍራዎች ውሱን በጣም ውሱን ሊሆኑ ነው፡፡ ደግሞስ የተቃውሞ ሰልፍ አንድም መንግስት እንዲሰማው ለማድረግ ሆኖ ሳለ፤ በመንግስት ተቋም አጠገብ መሰልፍ አይቻልም የሚሉት ደንብ እንዴት ያለ ደንብ ነው፡፡ ተቃጠልን እኮ ጎበዝ፡፡
የአንድነት የሶስት ወር ዘመቻ
6-   እንግዲህ በዚህ ሁሉ ሕገመንግስቱን የሚሸራርፉ የተጻፉ ደንቦችና አዋጆች፤ ያልተጻፉ አፋናዎችና ትንኮሳዎች ውስጥ ተሸሎክሉከው ነው፤ አንድነቶችና ሰማያዊዎች የተቃውሞ ሰልፎችን የሚያደርጉት፡፡ አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ፤ (ከዚህ በኋላ አንድነት እያልኩ ነው የምጠራው)፤ በቀጣዮቹ ሶስት ወራት ውስጥ ከአዲስ አበባ ተጀምሮ አዲስ አበባ የሚያበቃ፤ በ15-17 ከተሞች የሚደረግ፤ የኑሮ ውድነትን፤ የሰብአዊ መብት ጥሰትና አፈናና፤ የመሬት ባለቤትንትን፤ የሚመለከቱ የተቃውሞ ሰልፎችን አሰናድቷል፡፡ አንድነት በተለያዩ ከተሞች ውስጥ የሚደርጋቸውን ሰልፎች በገንዘብ ለመርዳት በውጭ አገር የሚገኙ የተለያዩ ከተሞች ኢትዮጵያዊያን ቃል እየገቡ ነው፡፡ መቼም ሲያትል ጎንደሬ ይበዛል፤ ጎንደርን ወስዷል፡፡ አትላንታ አንድ ከተማ ወስዷል፡፡ ላስ ቬጋስም እንደዚያው፡፡ እስካለፈው ወር መጨረሻ ድረስ የቀሩት ከተሞች አምስት ብቻ ናቸው፡፡ የቶሮንቶ አንድነት የድጋፍ ሰጪ ማህበርም የነቀምት ከተማን ሰለፍ ለመርዳት ቃል ገብቷል፡፡ ቀደም ሲል እሁድ ማርች 23 ቀን የአንዱዓለም አራጌን መጽሀፍ ለማከፋፈልና እስረኞችን ለማሰብ በተጠራ ዝግጅት ላይ የዝግጅቱ አስተባባሪ አቶ ታምራት ይገዙ ቶሮንቶ መቀሌንም ስፖንሰር እንደሚያደርግ አስታወቋል፡፡ ስለዚህ፤ ቶሮንቶ ሁለት ከተሞችን ስፖንሰር ያደርጋል ማለት ነው፡፡ ይሄ በረከት ሲያንሰን ነው፡፡
እነሆ ቅስቀሳ፤ አጋርነት ለነቀምት፤
7-   አንድነት ቶሮንቶ፤ ለነቀምቱ ሰልፍ የሚሆን ገንዘብ ለማሰባሰብ እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር ቅዳሜ ኤፕሪል 26 ቀን፤ ከሰዓት በኋላ፤ ከ3pm ሰኣት ጀምሮ፤ 2050 ዳንፎርዝ ጎዳና ላይ በሚገኘው ሂሩት ካፌ፤ የአብረን እንዋል መርሀግብር አዘጋጅቷል፡፡ ይሄ ጽሁፍ በከፊል የዚያ ዝግጅት ቅስቀሳ አካል ነው፡፡ ልቀስቅሳችሁ ተዘጋጁ፡፡ ቅስቀሳው እንዲህ የሚል ነው፤ አገር ቤት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን፤ ከላይ የጠቀስናቸውን መሰናክሎች አልፈው የተቃውሞ ሰልፍ ለማዘጋጀት ደፋ ቀና ሲሉ፤ ሰልፋቸው በኢህአዴግ ሰራዊት ወይም ፖሊስ ወይም ደህንነቶች እንጂ፤ በገንዘብ እጦት ምክንያት እንዳይሰናከል የማድረግ ግዴታ አለብን የሚል ነው፡፡ በቶሮንቶ አካባቢ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን፤ በዚህ መደበኛ ባልሆነ፤ የአብረን እንዋል ዝግጅት ላይ በመገኘት፤ የበኩላችንን የገንዘብ ልገሳ እንድናደርግ ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ፤ ቅዳሜ ኤፕሪል 26 ቀን፤ 2014 ዓ.ም፤ ከሰኣት በኋላ፤ ሂሩት እንገናኝ፡፡
8-   በነገራችን ላይ፤ ቶሮንቶ በቆየሁባቸው ያለፉት 13 ወራት፤ ከገንዘብ ማሰባሰብ ጋር በተያያዘ ቶሮንቶ የሚንቀሳቀሰው ከአቅም በታች ነው ማለት ይቻላል፡፡ ትንሽ ቋጣሪ መስሎብኛል፡፡ በርግጥም በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በሚደረጉ ፖለቲካ ነክ ዝግጅቶች ላይ የሚታደሙትንና ያላቸውን የሚወረውሩት ቸሮች፤ ተመሳሳይና የተወሰኑ ሰዎች በመሆናቸው፤ የዚህ ከአቅም በታች የመንቀሳቀስ ተጠያቂዎች እነማን እንደሆኑ እንጃ፡፡ ላለፈው ስርየት ሆኖ፤ ስለሚመጣው ሳስብ ግን፤ እኔ እንዲህ ያለውን አገራዊ ዝግጅት የማየው እንደበረከት ነው፡፡ ይሄ በረከት ለሁላችሁም መድረስ አለበት፡፡ ስለዚህ የመጪው ኤፕሪል 26፤ የአንድነት በረከት እንዳያመልጣችሁ፤ ሂሩት ካፌ እንገናኝ፡፡ በእለቱ በተለያየ ምክንያት መገኘት ያልቻለም፤ የገንዘብ ልገሳውን በሰው መላክ እንደሚችል ወይንም በአንድነት ባንክ ሂሳብ Unity for Human Rights and Democracy: TD Trust; የባንክ ሂሳብ ቁጥር፡ 12682 0041 0883 5209213 መክተት እንደአማራጭ እንደተቀመጠ፤ አንድነት ቶሮንቶ ያወጣው መግለጫ ያሳያል፡፡
ከደሴ ወደአዲስ፤ … ወደነቀምት፤ በዚህ 22 አመት እንደነቀምት የተጎዳ ማን አለ፤
9-   በርግጥ የአንድነት የአዲስ አበባ ሰልፍ በተያዘለት ቀን መጋቢት 28 አልቀጠለም፡፡ ይሄ ጽሁፍ ወደህትመት ሲላክ፤ የአዲስ አበባው ሰልፍ ሚያዚያ 5 እንደሚደረግ ቢገመትም፤ አሁን ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ፤ የአዲስ አበባ መስተዳድር ሰልፉ ቅዳሜ፤ የሰልፉም አቅጣጫ ወደጃንሜዳ ካልሆነ እያለ ነው፡፡ ማደናበር፤ ማናደድ፤ ማዘናጋት ይሉታል ይሄንን ስልት፡፡ እኔ፤ ብልጥ ልጅ የሰጡትን ይዞ ያለቅሳል ነው የምለው፡፡ ፖለቲካና ሕይወት ,ባልመረጥነው መንገድ ውስጥ የመረጥነውን ለማግኘት የምናደርገው ሩጫ ነውና፡፡ መጋቢት 28 ቀን በደሴ የተደረገው ሰልፍ ደማቅና የሚያበረታታ፤ በርግጥም ለሌሎች ከተሞችም መነሳሳትን የሚያመጣ እንደሆነ አስተውያለሁ፡፡ ስለዚህ፤ ነቀምትን ከደሴ የተሻለ ለመቀስቀስና ለማሰለፍ፤ ሁላችንም መረባረብ እንዳለብን ቀስቃሽ አያስፈልገንም፡፡ ደግሞስ በዚህ 22 አመት በኦነግ ስም እንደነቀምት የተጎዳ ማን አለ፡፡ ስለዚህ ነቀምት ተሰልፎ እሪይ ይል ዘንድ ግድ ነው፡፡ ደሴ ነቅሎ ወጥቷል፡፡ ነቀምትም ነቅሎ ይወጣል፡፡ ነቀምት ነቅሎ እንዲወጣም እኛም ከዚህ ከቶሮንቶ ነቅለን እንወጣለን፡፡ ቅዳሜ፤ ሚያዚያ 26 ቀን፤ ከሰዓት በኋላ፤ ከ3 እስከ 6 ሰዓት ሂሩት እንገናኝ፡፡
10-  ለተጨማሪ የአንድነት ዝርዝር አገልግሎቶችና መረጃዎች በአካል በአንድነት በጽህፈት ቤታት፤ ወይም ከታች በተጠቀሱት የመገናኛ መንገዶች ያግኙን፡፡ አንድነትን ለማግኘት፤ ኢሜል፤ unityforhumanrights@gmail.com ፤ ድረገጽ፤ http://andnettoronto.blogspot.ca/. የጽህፈት ቤት አድራሻ፡ B2- 2017 Danforth Avenue, Toronto, ዳንፎርዝ ላይ፤ ከዉድባይን ባቡር ጣቢያ በስተምስራቅ 50 ሜትር ራቅ ብሎ፤ ከዘመን እንጀራ መደብር በተቃራኒ፤ ከትብብር መረዳጃ እድር ጎን፡፡

Tuesday, 8 April 2014

ESAT Kignit Negash Gebru 08 April 2014 | ESAT Tube

ESAT Kignit Negash Gebru 08 April 2014 | ESAT Tube

ESAT Yesamintu Engeda Birhane Mewa April 2014 Part 3 | ESAT Tube

ESAT Yesamintu Engeda Birhane Mewa April 2014 Part 3 | ESAT Tube

የኢትዮጵያ ሽግግር ምክር ቤቱ ኢፕሪል 13 ስብሰባን በተመለከተ

April 7th, 2014
የአንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ንቅናቄ በሚል የጀመረው እንቅስቃሴ፣ በዉጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ድጋፍ እያገኘ መጥቷል። ኢትዮጵያዉያን በአካባቢያቸው ካሉ የአንድነት ድጋፍ ማህበራት ጋር በመሆን ከሚደግፉት በተጨማሪ፣ የተለያዩ ሲቪክ ማህበራት፣ በዉጭ አገር ያሉ የፖለቲካ ደርጅቶች እንዲሁም ግለሰቦች ሳይቀር፣ ጉዳዩ የአንድ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን የሕዝብ ጉዳይ ነው፣ በሚል ከሚሊዮኖች አንዱ ነን እያሉ ነው።

ENTC-flyer
ከነዚህ፣ አገር ቤት እየተደረገ ያለዉን እንቅስቃሴ ከሚደግፉ ድርጅቶች መካከል፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት አንዱ ነው። ምክር ቤቱ የራሱ አላማና ግብ ይዞ እየተንቀሳቀስ ያለ ደርጅት ነው።
በኢትዮጵያ የሚደረገዉን ሰላማዊና ሕጋዊ እንቅስቃሴ ምክር ቤቱ እንደሚደግፍ ብዙ ግዜ አሳዉቋል። አገር ቤት የሚደረገዉን ትግል የምክር ቤቱ መሪዎችና አባላት ያሳነሱበት፣ ያንቋሸሹበት፣ «አይሰራም፣ ጊዜ ማጥፋት ነው» በሚል በተዘዋዋሪ መንግስት ሕዝቡ ድጋፍ እንዳይሰጥ የሞከሩበት ጊዜ የለም። ይልቅስ ፣ የሽግግር ምክር ቤቱ፣ በዳያስፖራ ያለው የሚሊዮኖች ንቅናቄ ግብረ ኃይል ተወካዮችን ልኮ አብሮ የሚሰራ ከመሆኑም ባሻገር፣ በተለያዩ መግለጫዎቹ አገር ቤት ለሚደረገው ትግል ያለውን ሶሊዳሪቲ በገሃድ ያሳየ ድርጅት ነው።
ለምሳሌ ኦክቶብር ፣ 2013 የሽግግር ምክር ቤቱ «በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረገዉን ትግል እንደግፋለን» በሚል ርእስ ያወጣዉን መግለጫ ማንበብ እንችላለን። መግለጫዉ «የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ለነዚህ ቆራጥ የፖለቲካ ድርጅቶች በተለይም ለሰማያዊ ፓርቲና የአንድነት ድርጅት አመራርና አባላቶች፤ እንዲሁም በየእስር ቤት ተወርውረው ለሚገኙት የኢትዮጵያ የክፉ ቀን ደራሽ ጀግኖች የድርጅት መሪዎችና ጋዜጠኞች፤ ያለንን ከፍተኛ አድናቆት ከመግለጽ ባሻገር፤ ይህንን ግፈኛ ስርአት በህዝባዊ አመጽ መታገልና ማስወገድ የድርጅታችን መርህ ከመሆኑ አኳያ ሙሉ ድጋፋችንን የምንሰጥ መሆኑን እናረጋግጣለን» ሲል ነው፣ አገር ቤት ላሉት ታጋዮች ምክር ቤቱ አጋርነቱን የገለጸው።
ምክር ቤቱ የአንድነት ፓርቲም ሆነ ሌሎች ሰላማዊ በሆነ መንገድ ታግለው፣ በምርጫ አሸንፈዉ፣ በሕጉ መሰረት ሕገ መንግስቱን አሻሽለው፣ ለሁሉም ዜጎች እኩል የሆነች፣ አንዲት፣ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ብትመጣ ፣ እንደ ማንኛዉም አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የሚመኙትና የሚናፍቁት ነው። ለዚህም ነው ድጋፋቸዉን እየሰጡ ያሉት።
ነገር ግን ነገሮች እንደተጠበቁ ላይሄዱ ይችላሉ። «በአገራችን ኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ቀዉስ የበለጠ እየከረረ፣ ኢሕአዴግ እርሱ ባወጣዉ ሕግ አልገዛም ብሎ፣ ሕገ ወጥና አምባገነናዊ እርምጃዎች በመዉሰድ ፣ ወደ አላስፈላጊ ደረጃ ከተኬደ፣ በኢትዮጵያ አናርኪ እንዳይፈጠር፣ ከወዲሁ አማራጭ መፍትሄ ማዘጋጀት ያስፈልጋል» ብለው በሽግግር ምክር ቤቱ የሚንቀሳቀሱ ወገኖች ያምናሉ። አሁን በስልጣን ላይ ያሉት አምባገነኖች ኢትዮጵያ እንድትፈራርስ ፍላጎት ሊኖራቸው ይችላል የሚል እምነት በመኖሩም፣ ከወዲሁ በተለይም በዉጭ ያለውን ኃይል በማሰባሰብና ወደ አንድ በማምጣት፣ ተጠባባቂ PLAN B ለማዘጋጃት እየሰሩ ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት የሚል ስያሜም ለራሳቸው የሰጡት በዚህ ምክንያት ነው። ስልጣን ለመጨበጥ ሳይሆን፣ ነገሮችን በፈራረሱበት ወቅት፣ የሽግግር መንግስት ተቋቁሞ አገራችን እንደ አገር የምትቀጥልበትን ሁኔታ ለማረጋገጥ።
አገር ቤት ያለዉ ትግል ተጨባጭ ዉጤት አምጥቶ፣ በኢሕአዴግ እና በተቃዋሚዎች መካከል መግባባት ተፈጥሮ፣ አሁን ያለው ሕገ መንግስት ተሻሽሎ፣ ነገሮች ሁላችንም እንደምንፈልገው ቢሄዱና የሽግግር መንግስት ምክር አላስፈላጊ ከመሆኑ የተነሳ ቢከስም፣ ሁላችንም የምንመኘው ነው። ነገር ግን ያ እስኪሆን፣ «ምናልባት» በሚል መጠንቀቁ አስተዋይነት ነው። ለዚህም ነዉ ጥረታቸው ሊደገፍና ሊበረታታ የሚገባው።
የሽግግር ምክር ቤቱ፣ የፊታችን ሚያዚያ 5 ቀን በዋሺንግተን ዲሲ ስብሰባ ያደርጋል። ስብሰባዉን ላይቭ በፓልቶክ፣ ወይንም፣ ቴሌኮንፈራንስ የሚተላለፍ ከሆነ ለመከታተል እሞክራለሁ። በዲሲ አካባቢ ያሉ ኢትዮጵያዉያን በአካል ስብሰባዉን እንዲካፈሉ፣ ጥያቄዎችን እንዲጠይቁ፣ ሃሳባቸውን እንዲገልጹም አበረታታለሁ። በአገር ጉዳይ ላይ መመካከርና መወያየት ምንጊዜም ጠቃሚ ነውና።
ስብሰባው፣ ብዙ ጊዜ በዳያስፖራ ከተለመደውና አሰልቺ ከሆነው፣ አገዛዙን ከማዉግዝና ከመስደብ ፖለቲካ ያለፈ፣ የተጨበጡና ሥራ ላይ ያተኮሩ፣ ኢትዮጵያዊያን ማሰባብስ የሚችሉ፣ በሰለጠነ መንፈስ የሚቀርቡ፣ አንኳር ቁም ነገሮችን ጉዳዮችን አንስቶ እንደሚወያይ ተስፋ አደርጋለሁ።

በዓረና ከፍተኛ አመራሮቸ፣አባሎችና ዓረና በጠራው ህዝባዊ ስብሰባ ተሳታፊዎች የተፈፀመው ኢ ሰብአዊ እንግልት – ብርሃኑ በርሄ (የዓረና ፕሬዘዳንት)

April 7th, 2014
ዛሬ እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ/ም ዓረና ትገራይ ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ በምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወንበርታ ወረዳ ጠርቶ ያካሄደ ሲሆን ከትናትና ጀምሮ ህዝቡን ወደ ስብሰባው እንዲመጣ የሚቀሰቅሱ አባሎችና አመራሮች ከድንጋይ ውርወራና የቡድን ረብሻ ባለፈ ከተከራዩት አልጋ አስወጥቶ ሌሌት የትም ተጥለው እንዲወድቁ ለማድረግ እጅግ ኢ-ሰብአዊ ተግባር መፈፀሙን ተገልፆ ነበር ፡፡ የአፅቢ ፖሊስ አባላቶቻችን ከተከራየትና ገንዘቡን ከፍለው የክፍሉ ቁልፍ ተረክበው በእጃቸው ከሚገኝ ቤት ካለወጣሁ በማለት ትናንት መጋቢት 27 ቀን 2006 ዓ/ም አቶ አምዶም ገ/ሰላሴ ፣ አቶ ስልጣኑ ሕሸ ፣ መም/የማነ ንጉሰ እስከምሽቱ 2፡30 በአፅቢ ፖሊስ በእስር ነበሩ ፡፡ በዚሁ ቀን የወረዳ አስተዳዳዎች የሚመሩት ለህዝብ የሚታደል በራሪ ፅሑፍ መቅደድና በአራና አባላት ላይ ድንጋይ በመወርበር ሲያውኩ ዛሬ ጥዋት ደግሞ ቦዘኔ ህፃናትና ምልምል ካድሬዎች ገብረ ማርያም የተባለው የታጠቁ ምልሻ ጭምር በዓራና አባላት ላይ መጠነ ሰፊ የማወክ ተግባር እንደጀመሩና ስብሰባው እንዳይካሄድ ከፍተኛ ጥረት እንዳደረጉ ተገልፆ ነበር ፡፡
ዛሬ ከሰኣት በሁዋላ የህዝብ ስብሰባው እንደተጠናቀቀ ደገሞ የአረና ከፍተኛ አመራሮችና አባሎች እንዲሁም በስብሰባው የተገኙ ወደ 61 የሚሆኑ ገበሬወች በአፅቢ ከተማ ፖሊስ ጣብያ ታስረዋል ፡፡ የእስሩ መነሻ ምክንያት ተደባዳቢ የወንጀለኞች ቡድን የአረና አባላትን ሲደበድቡና ስብሳባው እንዳይጀመር ሲያውኩ የሚያሳይ መረጃ በሞባይል ቀርፃችሁዋል የሚል ሆኖ ተቀረፀ የተባለው ፊልም ከተገኘበት የሞባይል ስልክ አውጥቶ ለመንጠቅና ለማጥፋት ያለመ ነው፡፡
የአቶ አብርሃ ደስታ ሞባይል ተወስዶ እየተፈተሸ ሲሆን የሌሎቹ የአረና ከፍተኛ የአመራር አባላትና አባላት ሞባይል ስልኮችም እንዲሁም በስብሰባው የነበሩ ገበሬዎች ሞባይል በፖሊስ ተነጥቆ በአፅቢ ፖሊስ ጣብያ እስር ቤት እየተፈተሸ እንደሆነ ቦታው ያሉ የአረና አባላት ሪፖርት አድርገውልኛል ፡፡
ሁኔታው ለትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘአማኑኤል ለገሠ በሞባይል ስልካቸው 0914 300868 ልክ ዛሬ እሁድ ከሰአቱ 9፡30 ደውየላቸው ስልኩን እንዳነሱ የምደውልላቸው ያለሁኝ ብርሃኑ በርሀ መሆኔን ገልጨ ልክ በኩሓ አፀያፊ እስርና መንግላታት በዓረና አባለት እየተፈፀመ እንዳለ ሪፖርት ሳደርግላቸው እኔን መሆኔን እንዳወቁ ወዲያው ስልካቸውን የዘጉብኝ እንዳይሆን ብየ ስልኩን እንዳይዘጉብይ በፍጥነት በአፅቢ ስብሰባ የሚያካሂዱ አባላቶቻችን መታሰራቸው ስነግራቸው ንግግሬን ሳልጨርስ ስልኩን ዘጉት ፡፡
ፖሊስ ወንጀል ስለመሰራቱ ማስረጃ የያዘለት ይሸልማል እንጂ ወንጀል መሰራቱን የሚያረጋግጥ መረጃ ለማጥፋት ፖሊስ የሚሰራ ከሆነ ይህ ዓይነቱ ፖሊስ የሰላም አባት ወይስ የወንጀል አባት እንበለው ?
አሁን በፖሊስ ምርመራ በአፅቢ ፖሊስ ጣብያ የሚገኙት 1- አቶ ስልጣኑ ሕሸ የዓረና የድርጅት ጉዳይ ሃላፊና የፅሕፈት ቤት ሃላፊ 2- አቶ ዓምዶም ገብረ ስላሴ የዓረና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ 3- አቶ አብርሃ ደሰታ የዓረና የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ አባልና ስራ አስፈፃሚ አባል 4- መም/ ታደሰ ቢተውልኝ የዓረና ማእከላዊ ኮሚቴ አባል 5- አቶ አስገደ ገብረ ስላሴ 6 – መም/የማነ ንጉሴ 7 አቶ ሃይለ ኪሮስ ታፈረ 8- መም/ ሃይለ 9 አቶ ቴወድሮስ 10 – መምህር ክፍሎም እና ሌሎች የአረና አባላትና 61 የስብሰባው ተሳታፊ የአከባቢው ገበሬዎች ናቸው፡፡
ዓረና ትገራይ ፓርቲ ይህንኑ ዘግናኝ የገዢው ፓርቲ የዓፈና ተግባር እንዲቃወምና እንዲያጋልጥ ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ፣ ለሰብአዊ መብት መከበር የሚሰሩ ተnማት ፣ በኢትዮጵያ ለሚሰሩ የውጭ መንግስታት ኢንባሲዎች እንዲሁም ድምፃቸው ለታፈኑ ድምፅ ለመሆን ለሚሰሩ የሃገር ውስጥና የውጭ ሚድያዎች ጥሪውን ያቀርባል ፡፡ በተጨማሪም እነዚህ የጠራራ ፀሃይ ወንጀለኛች በሕግ ፊት ለመፋለም ይረዳ ዘንድ የቻለ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ለዓረና ትገራይ ፓርቲ የገንዘብና የሙ ድጋፍ እንዲያደርጉ ለሁሉም ወንጀል የሚፀየፉ ወገኖች ጥሪውን ያቀርባል ፡፡
ይህ ዓይነቱ ዓይን ያወጣ ወንጀል የትግራይ ህዝብ ከደርግ አፈና ለመታደግ በ 17 የትጥቅ ትግል ዓመታት ሂወታቸውና ንብረታቸው ለከፈሉ በሂወት ያሉ ለውጥ ፈላጊዎቹ የህወሓት አባለትና ደጋፊዎች እንዲሁም መላ የትግራይ ህዝብ በአማራጭ ሰላማዊ ትግል ለሚያካሂድ ፓርቲ የሚፈፀም ጭፍጨፋ በእራሱ መብት የተቃጣ ወንጀል መሆኑን አውቆ ብምሬት እንዲቃወመው ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ጭፍን ዓፈና የነፃት ባለ ራአዮችን በማጠናከር የነፃነት ራእይ ገዳዮችን የሚያዳክም ግብዝ ውሳኔ መሆኑን የትግራይ ህዝብ አኩሪ ፀረ ባእዳዊ ገዥዎችና ፀረ ፋሽት ደርግ ተጋድሎ በሚገባ ያስተማረን በመሆኑ በዚሁ እኩይ የደርግን አሻራ የወረሱ የአምባገነኖች ተግባር ዓረና ፓርቲና አባላቱ እንደማይንበረከኩ ሁሉም ሊያቀው ይገባል ፡፡ የዓረና ሃገራዊ ራኢ የሃገር አጀንዳ ሆኖ በሃረዊ ለውጥ ይደምቅ ዘንድ ዓረና ጠንክሮ እንደሚሰራም ደግሞ ያረጋግጣል ፡፡
ዓረና ትገራይ ፓለዴሞክራሲና ለሉእላዊነት ፓርቲ
መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ/ም ከቀኑ 10፡20

አንድነት የጠራዉን የደሴዉ ሰላማዊ ሰልፍ ቪዲዮ ይመልከቱ !

Monday, 7 April 2014

በደሴ ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ

April 6, 2014
UDJ party demonstration in Dese
አንድነት ፓርቲ “የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪ መፈክር በተለያዩ ከተሞች የሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደረግ ባሳወቀው መሰረት ዛሬ በደሴ ከተማ ብዙ ሺህ ህዝብ አደባባይ ወጥቶ ድምጹን ሲያሰማ ውሏል።
በተቃውሞ ሰልፉ ላይ ከተስተጋቡት መፈክሮች ውስጥ ጥቂቶቹ፣
- መሬት ከካድሬው ወደ ህዝቡ ይመለስ
- አንድነት ኃይል ነው
- የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ
- መሬት ለህዝብ ይመለስ
- ጭቆና በቃን
- ድል የህዝብ ነው
- በግፍ የታሰሩ ይፈቱ
በሰላማዊ ሰልፉ ማብቂያ ላይ የአንድነት ፓርቲ ተ/ም/ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለ፣ የአንድነት ፓርቲ ውጪ ጉዳይ ኃላፊ ኢ/ር ዘለቀ ረዲ እንዲሁም የአንድነት ፓርቲ የደሴ ሰብሳቢ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በህወሃት/ኢህአዴግ ማስፈራሪያ ሳይሸበር አደባባይ ወጥቶ ድምጹን ያሰማውን የደሴና አካባቢውን ህዝብ አመስግነዋል።