
ከዚህ በፊት የሽብር ወንጀል ለመፈጸም በማቀድ በሚል የዕድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት ወጣቱ ፖለቲከኛ እነአንዷለም አራጌና ሌሎች ፍርዱን ባለመቀበል ለታሪክና ለሕዝብ ፍርድ ለመተው ጉዳዩን ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት ወስደውታል፡፡ ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው ለማረጋገጥ እንደቻልነው ሰበር ሰሚ ግራና ቀኙን በመመልከት ሚዛናዊ ፍርድ ይሰጣል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡
ገዢው ፓርቲ “ሽብርተኛ“ ብሎ ያሰራቸው ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች በተለያዩ ዓለማቀፍ ተቋማትና ሚዲያዎች የዓመቱ ምርጥ ሰው ተብለው እየተመረጡና የተለያዩ የክብር ሽልማት እንዳሸነፉ በተለያዩ ሚዲያዎች መዘገቡ ይታወቃል፡፡
ነገ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት የፍርድ ሂደቱን መከታተልና ለእስረኞችም አጋርነቱን መግለጽ ይችላል።
No comments:
Post a Comment