Friday, 11 April 2014

ዜና ዕረፍት: የአሞራ አባት በድንገት አረፉ! – አብረሃ ደስታ በፌስ ቡክ እንደዘገበው

የጀግናው “አሞራ” አባት አቶ ነጋሽ ገብረሩፋኤል መጋቢት 20, 2006 ዓም በ80 ዓመታቸው በድንገት ማረፋቸው ታውቋል። አቶ ነጋሽ ወንድ ልጆቻቸው ለህዝብ ነፃነትና ደህንነት ሲሉ የህይወት መስዋእትነት በመክፈላቸው ምክንያት የሚረዳ አጥተው ባላቸው ዓቅም ሰርተው ለመብላት ዕንጨት ሲቆርጡ ድንገት ወድቀው ተጎድተው ለሕክምና የሚደርስላቸው ወገን በማጣታቸው ምክንያት ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል። አቶ ነጋሽ በትግራይ ማእከላዊ ዞን ቆላ ተምቤን ወረዳ ኗሪ ነበሩ። የአሞራ የትውልድ ቦታ ቆላ ተምቤን በህወሓቶች ከተበደሉ ወረዳዎች አንዷ ነች። ያከባቢው ኗሪዎች “ዓረና” እየተባሉ የመንግስት አገልግሎትና መሰረተ ልማት ተነፍገዋል። ፍትሕ አጥተዋል።
የኢቲቪ ጋዜጠኞች በወረዳው አስተዳዳሪዎች ታጅበው ከአቶ ነጋሽ ጋር (ለፖለቲካ ጥቅም) ቃለመጠይቅ ለማካሄድ ወደ ቆላ ተምቤን ተጉዘው ጉሮሮ በምትባል ትንሽ የገጠር ከተማ ሲደርሱ የአቶ ነጋሽን ሕልፈት ሲሰሙ በስርዓተ ቀብሩ ሳይገኙ ተመልሷል። ህወሓት አቶ ነጋሽን የሚፈልጋቸው ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ ነበር ማለት ነው። የአቶ ነጋሽ ሞት በኢቲቪ አልተነገረም።
ህወሓቶች የልጃቸው አሞራን ታሪክና ጀግንነት ለፖለቲካ ፍጆታ ከማዋል ያለፈ ዕርዳታ አድርገውላቸው እንደማያውቁ ያከባቢው ኗሪዎች ገልፀዋል። የተሰው ልጆቻቸው መሬት በህወሓቶች ተነጥቀዋል። “አሞራ ፊልም” ሲሰራ አቶ ነጋሽ ቃለ መጠየቅና ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ቃል ተገብቶላቸው ሲያበቃ ለህወሓት መሪዎች ጥቅም ሲባል ቃለ መጠይቁ ሲካሄድ ለአቶ ነጋሽ የተደረገ ድጋፍ ግን አልነበረም። ይልቁንስ የልጆቻቸው መሬት ተነጥቆ ለሌሎች ካድሬዎች ተሰጥቷል።
ለፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ሲባል ስለ አሞራ ታሪክ ይተረካል። አሞራ ያን መስዋእት ከፍሎ በሆነ ተአምር በህይወት ተርፎ አሁን “ለዴሞክራሲና ነፃነት ነበር የታገልኩትና የፈለኩትን ፓርቲ እደግፋለሁ፣ ያልፈለኩትን ፓርቲ ደግሞ እቃወማለሁ” ብሎ ዓረናን ቢደግፍ ኑሮ ከሃዲ ተብሎ በህፃናት በድንጋይ ይወገር ነበር። አሞራ እንኳን ጓዶች ህን እነ ስየና አስገደ አላየኋቸውም። በቃ በል በሰላም ተኛ።
የአቶ ነጋሽን ነፍስ በገነት ያኑርልን። ለቤተሰቦቻቸውን ፅናቱ ይስጥልን። R.I.P

No comments:

Post a Comment