June 3rd, 2014
ትዝ ይለኛል በ1997 ዓ.ም ይወጡ ከነበሩ ፕሬሶች ‹‹ነፃነት›› ጋዜጣ ትመስለኛለች በፊት ለፊት ገጽዋ ‹‹ንቢቱ መናደፍ ጀመረች!!›› የሚል ርዕስ ይዛ ነበር፡፡ የመለስን ‹‹እንከን የለሽ ምርጫ እናካሂዳለን›› የአደባባይ ቃል በጥይት ለመቀልበስ ሲሞከር የተሰጠ ርእስ ነበር፡፡
እነዚህ ሰዎች በርግጥም ዴሞክራሲን በወረቀት እንጂ በተግባር ለማረጋገጥ አልቻሉም፡፡ በአንድ እጃቸው ምዕራባዊያን እንዳይከፋቸው ዴሞክራሲን በሌላ እጃቸው ደግሞ የዴሞክራሲ መቀልበሻ ክላሽ ይዘው 23 ዓመታትን አስቆጥረዋል፡፡
አሁንም ዴሞክራሲንና ክላሽን አንግተው ሁለቱንም እንዳስፈላጊነቱ እየተጠቀሙ ይገኛሉ፡፡ ሁለቱ ግን ፈፅሞ የሚቀላቀሉ አይደሉም፡፡ ከሁለቱ አንዱን መምረጥ ያስፈልጋል፡፡ ኢህአዴግም አንዱን መምረጥ አለበት፡፡
አንደኛው ምርጫ ክላሹን ለድንበር መጠበቂያ ብቻ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ሳይሸራረፍ እንዲረጋገጥ ማድረግ ነው፡፡ አፈና፣ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ፣ እስርና ግድያን በማቆም ስልጣን ከምርጫ ኮሮጆ ብቻ እንዲወጣ ማድረግ ነው፡፡
ይህንን ማድረግ ካልቻለ ሁለተኛ ምርጫም አለው፡፡ ደፈር ብሎ ‹‹ከዚህ በኋላ ምርጫ፣ መድብለ ፓርቲ፣ ነፃ ፕሬስ፣ በነፃ መደራጀት፣ መቃወም አይቻልም፡፡ መፃፍም አይቻልም፡፡ ያለውም አንድ ፓርቲ ብቻ ነው፡፡ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ወይም ሞት…›› የሚል አዋጅ አውጆ ቢያርፈው፡፡ ሶቅራጥስ እንዳለው ዓለም በሁለት ተቃርኖዎች ውስጥ ናት፡፡ ኢህአዴግም ከሁለቱ ተቃርኖዎች (ዴሞክራሲና ጠመንጃ) አንዱን መምረጥ አለበት፡፡ እኛም ቁርጡን አውቀን እንቀመጥ ነበር፡፡
Wednesday, 4 June 2014
ሕድሮም: ህወሓት የፖለቲካ አማካሪየን ሊታስርብኝ ነው
June 4th, 2014
ጓዶች ዓረና ባደረገው እንቅስቃሴ በትግራይ ክልል ሙሉ ድጋፍ እንዳለው አረጋግጧል። ይሄን ጉዳይ ህወሓትም ተረድቶታታል። እናም የህወሓት አመራር አባላት ዓረናን ለማዳከም አባላቶቻችን በጥቅም በመደለል፤ ካልተሳካ ደግሞ በማስፈራራት እንዲሁም በድንጋይ በመውገር ህዝብን የማነሳሳት እንስቅስቃሴያቸው እንዲያቆሙ ለማድረግ ሞክረዋል። አልሆነም። እናም አሁም የዓረና አባላትን (አስተባባሪዎችን) ለማሳሰር ዉሳኔ ተላልፈዋል። አሁን በግፍ ማሰር ጀምረዋል። አባላትን በማሳሰር ዓረናን ማዳከም ግን አይቻልም። ምክንያቱም ዓረና በህዝብ ልብ ገብቷል። ሁላችንም ቢያጠፉን እንኳ ዓረናን ማሸነፍ አይችሉም። አሁን በደረሰኝ መረጃ መሰረት በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ህዝብን ያነሳሳና ከአንድ ወረዳ አንድ ሺ አምሳ ሁለት (1052) አባላትን ያፈራ የዓረና ጀግና አቶ ሕድሮም ሀይለስላሴን ለማሳሰር ወስነዋል። የሕድሮም ተባባሪዎች ናቸው የተባሉትና እንዲታሰሩ የተወሰነባቸው የሚከተሉት ናቸው።
“በሰበብ አስባቡ” እንዲታሰሩ ዉሳኔ የተላለፈባቸው የአፅቢ ወንበርታ ወረዳ የዓረና አስተባባሪዎች:
(1) ሕድሮም ኃይለስላሴ
(2) ሓምሳለቃ ኪሮስ ሓደራ
(3) አስራለቃ ክንፈ ገብረህይወት
(4) አቶ ወልደገብር ኤል ኃይሉ
(5) ወይዘሮ አለማት ብርሃን ገብረገርግስ
በደረሰኝ መረጃ መሰረት እነኚህ ሰዎች ይታሰራሉ። ምናልባት ያልሰሙ ከሆነ ተገቢውን ጥንቃቄ ይደረግ። የሚታሰሩበት መንገድ “በሰበብ አስባቡ” ነው የሚለው። ስለዚህ በፍርድቤት ክስ ተመስርቶ በፍርድቤት ዳኛ ላይ ተፅዕኖ በመፍጠር ሊከናወን ይችላል። በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ብዙ ዳኞች ከስራቸው ተባረዋል። ፍትሕን ለማስፈን ጥረት በማድረጋቸው፤ በካድሬዎች ትእዛዝ ሳይሆን በሕገ መንግስት መሰረት ነው የምንፈርደው በማለታቸው ምክንያት። ዳኛ ካሕሳይ ዘገየ ጥሩ ምሳሌ ነው።
ሕድሮም ኃይለስላሴ አርሶአደር ሲሆን የታጋይ ልጅም ነው። አባቱ አቶ ኃይለስላሴ አሰፋ የቀድሞ የህወሓት ታጋይ ሲሆን ተሰውቷል። አቶ ሕድሮም አሁንም ለነፃንቱ የሚታገል ጀግናችን ነው። የፖለቲካ አስተማሪዬ ነው። ሌሎቹ ደግሞ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች ሲሆኑ አሁንም የነፃነት ትግላችን በሸፍቶች ተጠልፏል ባዮች ናቸው። ወደ ህወሓት ከመቀላቀላቸው በፊት በደርግ ስርዓት በደል ይደርስባቸው እነደነበረና አሁን ተመሳሳይ ግፍ እንደሚፈፀምባቸው ይናገራሉ። በዓረና ለዓረና እየታገሉ ብዙ ሰዎች ከጎናቸው ያሰለፉ ጀግኖች ናቸው።
ሕድሮም ኃይለስላሴ የፖለቲካ መምህሬና አማካሪየ ነው።
ሕድሮም! It is so!!!
ጓዶች ዓረና ባደረገው እንቅስቃሴ በትግራይ ክልል ሙሉ ድጋፍ እንዳለው አረጋግጧል። ይሄን ጉዳይ ህወሓትም ተረድቶታታል። እናም የህወሓት አመራር አባላት ዓረናን ለማዳከም አባላቶቻችን በጥቅም በመደለል፤ ካልተሳካ ደግሞ በማስፈራራት እንዲሁም በድንጋይ በመውገር ህዝብን የማነሳሳት እንስቅስቃሴያቸው እንዲያቆሙ ለማድረግ ሞክረዋል። አልሆነም። እናም አሁም የዓረና አባላትን (አስተባባሪዎችን) ለማሳሰር ዉሳኔ ተላልፈዋል። አሁን በግፍ ማሰር ጀምረዋል። አባላትን በማሳሰር ዓረናን ማዳከም ግን አይቻልም። ምክንያቱም ዓረና በህዝብ ልብ ገብቷል። ሁላችንም ቢያጠፉን እንኳ ዓረናን ማሸነፍ አይችሉም። አሁን በደረሰኝ መረጃ መሰረት በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ህዝብን ያነሳሳና ከአንድ ወረዳ አንድ ሺ አምሳ ሁለት (1052) አባላትን ያፈራ የዓረና ጀግና አቶ ሕድሮም ሀይለስላሴን ለማሳሰር ወስነዋል። የሕድሮም ተባባሪዎች ናቸው የተባሉትና እንዲታሰሩ የተወሰነባቸው የሚከተሉት ናቸው።
“በሰበብ አስባቡ” እንዲታሰሩ ዉሳኔ የተላለፈባቸው የአፅቢ ወንበርታ ወረዳ የዓረና አስተባባሪዎች:
(1) ሕድሮም ኃይለስላሴ
(2) ሓምሳለቃ ኪሮስ ሓደራ
(3) አስራለቃ ክንፈ ገብረህይወት
(4) አቶ ወልደገብር ኤል ኃይሉ
(5) ወይዘሮ አለማት ብርሃን ገብረገርግስ
በደረሰኝ መረጃ መሰረት እነኚህ ሰዎች ይታሰራሉ። ምናልባት ያልሰሙ ከሆነ ተገቢውን ጥንቃቄ ይደረግ። የሚታሰሩበት መንገድ “በሰበብ አስባቡ” ነው የሚለው። ስለዚህ በፍርድቤት ክስ ተመስርቶ በፍርድቤት ዳኛ ላይ ተፅዕኖ በመፍጠር ሊከናወን ይችላል። በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ብዙ ዳኞች ከስራቸው ተባረዋል። ፍትሕን ለማስፈን ጥረት በማድረጋቸው፤ በካድሬዎች ትእዛዝ ሳይሆን በሕገ መንግስት መሰረት ነው የምንፈርደው በማለታቸው ምክንያት። ዳኛ ካሕሳይ ዘገየ ጥሩ ምሳሌ ነው።
ሕድሮም ኃይለስላሴ አርሶአደር ሲሆን የታጋይ ልጅም ነው። አባቱ አቶ ኃይለስላሴ አሰፋ የቀድሞ የህወሓት ታጋይ ሲሆን ተሰውቷል። አቶ ሕድሮም አሁንም ለነፃንቱ የሚታገል ጀግናችን ነው። የፖለቲካ አስተማሪዬ ነው። ሌሎቹ ደግሞ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች ሲሆኑ አሁንም የነፃነት ትግላችን በሸፍቶች ተጠልፏል ባዮች ናቸው። ወደ ህወሓት ከመቀላቀላቸው በፊት በደርግ ስርዓት በደል ይደርስባቸው እነደነበረና አሁን ተመሳሳይ ግፍ እንደሚፈፀምባቸው ይናገራሉ። በዓረና ለዓረና እየታገሉ ብዙ ሰዎች ከጎናቸው ያሰለፉ ጀግኖች ናቸው።
ሕድሮም ኃይለስላሴ የፖለቲካ መምህሬና አማካሪየ ነው።
ሕድሮም! It is so!!!
