Thursday, 23 January 2014

አንድነት – እነ አንዷለም አራጌ ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው አቶ አንዷለም አራጌ፣ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ናትናኤል መኮንን እንዲሁም አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ ነገ ጥር 16 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርቡ ታወቀ፡፡
andu_udj
ከዚህ በፊት የሽብር ወንጀል ለመፈጸም በማቀድ በሚል የዕድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት ወጣቱ ፖለቲከኛ እነአንዷለም አራጌና ሌሎች ፍርዱን ባለመቀበል ለታሪክና ለሕዝብ ፍርድ ለመተው ጉዳዩን ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት ወስደውታል፡፡ ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው ለማረጋገጥ እንደቻልነው ሰበር ሰሚ ግራና ቀኙን በመመልከት ሚዛናዊ ፍርድ ይሰጣል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡
ገዢው ፓርቲ “ሽብርተኛ“ ብሎ ያሰራቸው ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች በተለያዩ ዓለማቀፍ ተቋማትና ሚዲያዎች የዓመቱ ምርጥ ሰው ተብለው እየተመረጡና የተለያዩ የክብር ሽልማት እንዳሸነፉ በተለያዩ ሚዲያዎች መዘገቡ ይታወቃል፡፡
ነገ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በመገኘት የፍርድ ሂደቱን መከታተልና ለእስረኞችም አጋርነቱን መግለጽ ይችላል።

No comments:

Post a Comment