Wednesday, 1 January 2014

የደቡብ ሱዳን ተፋላሚዎች ለድርድር መዘጋጀት

ቀን 01.01.2014

የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች ልዑካን ወደ 3 ሳምንታት ከተጠጋ የአርስ በርስ ውጊያ በኋላ ለሰላም ድርድር ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ መግባታቸው ተነግሯል።
የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት IGAD አባል ሃገራት ናይሮቢ ላይ ቀደም ሲል ተወያይተዉ ሁለቱ ወገኖች ተኩስ በማቆም ለሰላም ድርድር እንዲዘጋጁ ባሳሰቡት መሠረት ተቀናቃኞቹ ወገኖች ለዉይይት መስማማታቸዉን አስታዉቀዋል።

በሰላሙ ውይይት፣ ቅድሚያ የሚሰጠው የተኩስ አቁሙን ስምምነት መቆጣጠር የሚቻልበት መላ ሳይሆን አይቀርም ።

 ዛሬ አዲስ አበባ ስለገቡት ደቡብ ሱዳናውያን ተደራዳሪዎችና ቀጣዩ እርምጃቸው ወደ ስቱዲዮ ከመግባታችን በፊት የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ፣ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን በስልክ አነጋግሬአቸው ነበር።
 

 

 

No comments:

Post a Comment