Sunday, 4 May 2014

የአዲስ አበባዉ ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ በላም ተጠናቀቀ ! ፎቶዎች ይመለከቱ

May 4th, 2014
የአዲስ አበባው ሰልፍ እጅግ በደመቀና በሚያምር ሁኔታ ተጠናቋል። የተወረረ ጠጠር የተጎዳ ሰው፣ የወደመ ንብረት አልነብረም። ምንም አይነት ግጭት ከፖሊሲ ጋር ያልተፈጠረ ሲሆን እጅግ በጣም ክብ የሚነኩ መፈክሮች ሲሰሙ ነበር።፡ ፎቶዎችን እንሆ !addis_demo
addisdemo2
addisdemo3
addisdemo4

ጥቂት የሰማያዊ አባላት በሰልፉ ላይ እንደ ሕዝቡ እንዲሆኑ ተጠየቁ

May 4th, 2014
የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ትላንት ማታ የአንድነትን ሰልፍ እንደሚቀላቀሉ በፌስቡክ ማሳወቃቸው ይታወቃል። ዛሬ ጠዋት ሰልፉ ከመጀመሩ በፊት የሰማያዊ ፓርቲ ሰማያዊ አርማ ያለበት ልብስ በመልበስና የሰማያዊ ፓርቲ አርማ በመያዝ፣ አስቀድመው የሰልፉን አዘጋጆች ሳያሳውቁ ወደ አንድነት ጽ/ቤት ጥቂት የሰማያዊ ወጣቶች ይመጣሉ።blue_udj1
የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በሰልፉ እንዳይሳተፉ በአንድነቶች ተከለከሉ የሚል አንዳንድ ትሽቶች በሰማያዊዎች በሶሻል ሜዲያዎች ተለቀዋል።
የሰማያዊ ፓርቲ፣ አንድነት ሰልፍ ለማዘጋጀት እየሞከረ ባለበት ወቅት ጣልቃ በመግባት፣ ለአንድነት ፓርቲ እውቅና ተነፍጎ ለሰማያዊ በመፈቀዱ፣ ሚያዚያ 19 ቀን ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወቃል። በሰልፉም ወደ 3፣ 4 መቶ የሚገኙ ዜጎች የነበሩ ሲሆን፣ በሰልፉም ወቅት ከፖሊስ ጋር ግብግብ እና ረብሻ መፈጠሩን የሚያሳዩ ቪዲዮዎችን ተመልክተናል።
የአንድነት የሰልፉ አዘጋጆች፣ ሰልፉን በሰላም እንዲጠናቀቅ ለመርዳት፣ አላስፈላጊ መፈክሮችና ባነሮች እንዳይንጸባረቁ፣ ከፖሊስ ጋር ግጭቶች እንዳይፈጠሩ፣ ብዙ ዝግጅቲች አስቀድመው ሲያደርጉ እንደነበረ የሚገልጹት የአንድነት አደራጆች፣ የሰማያዊ ፓርቲ በኦፊሴል ሰልፉን እንደሚቀላቀሉ የገለጹበት ሁኔታ እንደሌለ አስረድተው፣ አስቀድሞ አብሮ መገናኘት ቢቻል ኖሮ መፈክሮችን ፣ ፋልየሮች፣ ቅስቀሳዎች አብሮ ማድረግ በተቻለ ነበር ሲሉ ያስረዳሉ።
ሰማያዎች በድንገት ከሰልፉ አዘጋጆች እውቅና ዉጭ፣ ከሌላው ህዝብ የተለየ፣ የሰማያዊ ፓርቲን አርማዎች ይዘው መምጣታቸው፣ ትክክል እንዳልነበረ ሰማያዊዎች በሚነገራቸው ጊዜ «አንድነት ሂዱልን አለን» በሚል በአንድነት ላይ ዘመቻ መክፈታቸው፣ አሳዛኝ እንደሆነ ይናገራሉ።
«ሰማያዊዎች ለምን አንድነትን እየተከታተሉ ረብሻ እንደሚፈጥሩ አይገባኝም። ያለፈው ሳምንት የነርሱ ሳምንት ነበር። ማንም በነርሱ ሥራ ጣልቃ አልገባም። አሁን ሌሎች ድርጅቶች በሚያዘጋጁት እንቅስቃሴ ላይ እንደ ሌላው ሕዝብ በአክብሮት መቀላቀል እንጂ፣ የሌሎችን ሥራ ለማበላሸት መሞከሩ ማን ይባላል ? » ሲሉ በሰማያዊዎች የታየው አፍራሽ ተግባር እንደሆነ ይናገራሉ።
«ከአንድነት ፓርቲም ሆነ ከሌሎች ጋር አብረው መስራት ከፈለጉ፣ መጀመሪያ ቪጂላንቲ ባህሪያቸውን መቀየር አለባቸው። ተቋማዊ መግባባት፣ መክበባር፣ ምን ማለት እንደሆነ መረዳት አለባቸው። በስሜት ሳይሆን በቁም ነገር በአመራር ደረጃ አብሮ መነጋገርና መመካከር ያስፈልጋል» ሲሉ የሰማያዊዎች «ሂዱልን ተባልን » የሲሻል ሜዲያ ዘምቻን አሳፋሪ ብለዉታል።
ዳዊት ሰለሞን የነበዉን ሁኔታ በዚህ መልክ አስቀምጦታል፡
« ዛሬ በተደረገው ሰልፍ ለመካፈል የሰማያዊ አምስት ወጣቶች የሰማያዊ ፓርቲ ስያሜና አርማ ያለበትን ቲሸርት በመልበስ ሰልፉ ከመጀመሩ ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብለው ወደ አንድነት ቅጥር ግቢ መጡ፣ ሰልፉን የሚያደራጁ የአንድነት አባላት በሰልፉ ስለሚለበስ ልብስ፣ስለሚያዙ መፈክሮችን በተመለከተ ቀደም ብለው ሲሰሩ ስለነበሩ የሰማያዊ አባላት የፓርቲውን ልብስ ለብሰው መምጣታቸውን በመመልከታቸው የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግኑኝነት የሆነውን ብርሃኑ ተክለያሬድን ለማናገር ጠራሁት። «ብርሃኑ በሰልፉ ለመካፈል ስለመጣታችሁ አክብሮት አለን ነገር። ግን ቲሸርቱን ለብሳችሁ እንደምትመጡ ብትነግሩን ጥሩ ነበር፡፡» አልኩት። ብርሃኑ አላስጨረሰኝም «መሄድ እንችላለን» አለኝ፡፡
«ያንን ማድረግ የራስህ ምርጫ ነው፣ ሂድ ሳይሆን ያልኩህ በእንዲህ አይነት መንገድ እንደምትመጡ ብትነግሩን መልካም ይሆን ነበር» አልኩት። እናም ከአራት ጓደኞቹ ጋር በመሆን ግቢውን ለቅቀው ሄዱ።፡ከደቂቃዎች በኋላ «114 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በአንድነት ሰልፍ እንዳይገኙ ተባረሩ» በማለት ማውራት ጀመሩ፡፡(መጥተው የተመለሱትን የሰማያዊ አባላት የሚያሳይ ፎቶግራፍም ለማስረጃነት ይመልከቱ፡፡)

በማእነደሁልጊዜው ሁሉ ህገ መንግስታዊ መብቶቻችን መጠየቅ እንቀጥላለን ሰርና በመደብደብና በመግደል የአገር ችግር አይፈታም !!!!!

May 4, 2014

ክቡራን የዞን ዘጠኝ ነዋሪያን


ሳምንቱ በአራማጅነት ቆይታችን ከነበሩን ጊዜያት መካከል በጣም ከባድ ሆኖ አለፈ። የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጅ ጋዜጠኛ ጓደኞቻችን ከታሰሩ 7 ቀናትን አሳለፋ፡፡ በሳምንቱ ውስጥ ቤተሰብና የህግ ባለሞያ ሳያገኛቸው እሁድ ቀን ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ከመስማት ውጪ አያያዛቸውንም ሆነ ያሉበትን የጤንነት ሁኔታ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ እስካሁንም ቤተሰብም ሆነ የህግ ባለሞያ እነዲያያቸው አልተፈቀደም፡፡ ይህ በግልጽ ህገ መንግስቱን የሚጥስ የምርመራ ሂደት በማእከላዊ ሲካሄድ አዲስ አይደለም፡፡ ከዚህ በፌት የነበሩ የፓለቲካ እስረኞችም በተመሳሳይ ሁኔታ የመታየት መብታቸው ከማእከላዊ ጀምሮ ተነፍጎ አሁንም ቤተብሰብም ሆነ ወዳጅ እነዳይጎበኛቸው የተደረጉ እንዳሉ ይታወቃል ፡። ዞን 9 ከመጀመሪያ ዘመቻዎች አንስቶም ህገመንገስቱ አንዲከበረ ስንጠይቅ መቆየታችን ይታወቃል፡። ይህ መሆኑ ሳያንስ የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን ሲጠቀሙ የነበሩ (ሶስተኛው የዞን ዘጠኝ ዘመቻ) የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች እስር የአካል ጉዳትና ሞት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ይህ በመላው አገሪትዋ እየታየ ያለውን ተቃውሞ መንግስት ምላሽ እየሰጠ ያለበት መንገድ አሳሳቢ አስፈሪና አሳፋሪ ከመሆኑም በላይ ሳምንቱንም በሰብአዊ መብቶች ረገድ በጣም የከፋ ያደርገዋል፡፡Zone 9 bloggers
መንግስት የዞንዘጠኝ አባላትንና ጋዜጠኞቸን ሰርተዋል ብሎ ያቀረበው ወንጀል በማህበረሰብ ሚዲያ በመጠቀም ህዝብን ለብጥብጥ ማነሳሳት ነው ሲል የመንግስት ቃል አቀባይ በበኩላቸው በጻፉት ሳይሆን በወንጀል በመሰማራታቸው ነው የታሰሩት ብለዋል፡፡ ወንጀሉ ፓሊስ እንዳቀረበው ደግሞ በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥን የማንሳት ተግባር ከአገር ውጨ ከሚገኝ ራሱን ከሰብአዊ መብት ብሎ ከሚጠራ ተቋም ጋር ተባብረው ብጥብጥ ማስነሳት ነው ብሎታል ፡፡ ክሱ በአጭሩ ሁለት ነገሮችን ይይዛል፡፡ አንደኛው በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ ማስነሳት ሲሆን ሁለተኛው በሃሳብና በገንዘብ ከውጪ ድርጅቶች ጋር መተባበር ነው ፡፡
ማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ?
በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ ማንሳት የሚል ክስ ለማቅረብ በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ የሚያስበሱ መልእክቶቸን ማስተላለፍ ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ ማንኛውም የዞን 9 ነዋሪያን እነደሚመሰክሩት ህገ መንግስታዊ መብቶች እነዲከበሩ ከመጠየቅና መንግስትን የሚተቹ ጽሁፎችን ከማቅረብ ባለፈ አንድም የዞኑ ስራ ለብጥብጥ እና ለሁከት ምክንያት ለመሆን የሚበቃም አይደለም፡፡ ይህንነ ለመረዳት የዞኑን ዘመቻዋች እና ጽሁፎች ማየት ብቻውን የክሱን አስቂኝነት ለማስረዳት ይበቃል፡፡ እስከዛሬ በጻፍናቸው የመንገስት ትችቶች ካልሆነ በስተቀር ባነሳሳናቸው ብጥብጦች አንታወቅም ፡፡ ለዚያም ነው በጽሁፋቸው አይደለም የታሰሩት የሚለውን የመንግሰት ማስተባበያ አስቂኝ የሚያደርገው ፡። በጽሁፍ ካልሆነ በምንድነው የዞን 9 አባላትን እንድ ላይ እንደቡድነ ሰብስቦ መክሰስ የሚቻለው??
ከውጨ ድርጅት ጋር መተባበር
ዞን 9 ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ላለፉት ሁለት አመታት በነበረው ቆይታ የተለያዩ አጋርነቶችነ ከተለያዩ አካላት ጋር ፈጥሮአል፡። በዚህም በተለያየ ጊዜ እነደግለሰብም አንደቡድን ተወካይ በመሆን አባላቱ አገሪትዋ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብጥ ጥሰት አያያዝ አስመልክቶ ለተለያዩ ቦታዎች ንግግር አድርገዋል፡፡ ኢንተርኔት ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደርጋቸውን አስተዋእጾም አስመልክቶ በቡድንም በነጠላም በተለያዩ ቦታቸዎች ላይ በመገኘት ልምዳቸውን አካፍለዋል፡፡ ይህ መንግስት ሲፈልግ የሚፈቅድላቸው ሲፈልግ ወንጀል የሚያስመስለው ተግባር ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጲያዊ ህገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡ ዜጎች በመጓዛቸው ስራቸውን እና ልምዳቸውን በማካፈላቸው እነዲሁም ራሳቸውን ብቁ በማድረግ የሚሰሩትን የሰብአዊ መብት እነቅስቃሴ ለሌሎች መናገራቸውን ወንጀል ለማስመሰል የሚደረገውን ጥረት አሁንም ቢሆን እንደዞን 9 አጥብቀን እናወግዛለን፡፡ ከዚህ በፌትም እነደተናገርነው በህግ እስካልተከለከለ ድረስ ህጋዊ እንቅስቃሴዎቸን መንግስት ስላልወደዳቸውና ህገ ወጥ ስላስመሰላቸው የምናቆምበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ሁሉም የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጆች በፓርላማ በህገ ወጥነት ከተፈረጁ ተቋማት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት አልነበራቸውም የላቸውምም፡። ለዞን ዘጠኝ ስራም ምንም አይነት የፋይናንስ ድጋፍ አግኝተን አናውቅም፡፡ (በመሰረቱ የፋይናንስ ድጋፍ የማያስፈልገው የበጎ ፍቃደኝነት ስራ ነው የምንሰራው ) ከዚያ ውጪ ግን በፓርላማ ህገ ወጥ እስካልተባሉ ወይም ከልካይ ህግ እስካልመጣ ድረስ ከተለያዩ በተባበሩት መንግስታት እውቅና ካላቸው የመብት ተሟጋች ተቋማት ጋር ያለንን ግንኙነት ወንጀል ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት አንቀበለውም፡።
አንዳንድ አስቂኝ የመንግስት ወዳጆች በህቡህ ተደራጅተው የሚል ክስም ሲለጥፉብን ሰምተናል፡፡ ህቡህ ማለት ምን ማለት እነደሆነ ትርጉሙን እንዲያጣሩ ከመጠየቅ ባለፈ ምንም የምንጨምረው ነገር የለንም ፡፡ ባለፉት ሁላት አመታት ቆይታችን ፎቶአችን የሚታይ ሙሉ ህጋዊ ስማችን የሚታወቅ አገር ውስጥ የምንኖር ኢንተርኔት ላይ የተናገርነውን በግንባር የምንደግም ህጋዊ ዜጎች ነን፡። ከዞን ዘጠኝ እሴቶች መካከልም አንዱ ለተናገሩትም ሆነ ለሚያስተላልፉት መልእክት ሙሉ ሃላፌነትን መውሰድም ጭምር ነው ፡፡ በመሰረቱ ኢንተርኔት ላይ ቡድን መመስረት በየትኛውም ህግ የማይከለከል ህጋዊ ተግባር መሆኑን ለመንግስትና የመንግሰት እርምጃ ለደገፉ ለማስታወስ አንወዳለን፡፡
ባለፉት ቀናት ስንናገር እንደነበረው መንግሰት የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጆችን እነዲፈቱ መጠየቁን አሁን ደግሞ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ በመቃወም በጋራ ድምጻችንን ማሰማታችንን እንቀጥላለን፡፡ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እየተደበደቡና እየሞቱ የዞን9 አባላትን እስር ብቻ ለይተን ዘመቻ ማድረጉን ሃላፌነት የሚሰማው ሆኖ አላገኘነውም፡፡ በመሆኑም ሁለቱ ጉዳዪች ላይ አተኩረን የሚመለከተው አካል ሃላፌነቱን እነዲወጣ ግፌት ለማድረግ እንሞክራለን፡። ዞን ዘጠኝ እንቅስቃሴን በማሰር ለመገደብ ቢሞክርም ብዙ የዞኑ ነዋሪያን ጋር በመተባበር ከምርጫ ጋር የተያያዙ ስራዎችን የመስራት እቅዳችነን አጠናክረን እንቀጥልበታለን፡።
ከነገ ሚያዝያ 25 ጀምሮ የዞን 9 ጦማርያንን እና ወዳጅ ጋዜጠኞችን መፈታት እነዲሁም በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የምን ቃወምበት መጠነ ሰፌ ዘመቻ እንጀምራለን፡፡ እስካሁን በተናጠል ላሳያችሁን ህብረት በከፍተኛ ሁኔታ እያመሰገንን በጋራ የአገራችንን “ዞን ዘጠኝተነት” በመቃወም ህብረታቸንን እናሳይ ፡።

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት አንድነት የጠራውን የሰላማዊ ሰልፍ እንደሚቀላቀሉ አስታወቁ

May 3, 2014
በተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች ታስረው የሰነበቱትና ቀሪዎቹ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ዛሬ ባደረጉት ሳምንታዊ የወጣቶች የውይይት ፕሮግራም አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) የ‹‹እሪታ ቀን›› በሚል የጠራውን ሰልፍ በግንባር ቀደምነት በመቀላቀል ድምጻቸውን እንደሚያሰሙ አስታውቀዋል፡፡
ወጣቶቹ ሰልፉን እንደሚቀላቀሉ ያስታወቁት ‹‹ሰላማዊ ሰልፉ ውጤታማ እንዲሆን በምን መልኩ ልናግዝ እንችላለን?›› በሚል አጀንዳ በተወያዩበት ወቅት ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ከውህደት በዘለለ በሰላማዊ ሰልፍም ሆነ በሌሎች የትግል ስልቶች መተባበርና አብሮ መስራት እደግፋለሁ የሚል አቋም እንደሚያራምድ በተለያዩ ሚዲያዎች መግለጹ የሚታወቅ ሲሆን ወጣቶቹ በሰላማዊ ሰልፉ የሚያደርጉት ተሳትፎ ፓርቲው ለትብብር ያለውን አቋም ያሳያል ብለዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ለሰላማዊ ሰልፉ ድምቀት የሚያገለግሉ ሜጋ ፎኖች፣ ጥሩምባዎችና ሌሎችም ሰልፉን ለማድመቅ የሚያገለግሉ መሳሪያዎችን ይዘው እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
Addis Ababa Semayawi party rally April 27, 2014