Friday, 2 May 2014

Sec Kerry travels to Ethiopia: will he bring up press freedom?

May 1, 2014
by Tom Murphy
Secretary of State John Kerry is in the midst of a week-long trip to three sub-Saharan African nations: Ethiopia, Democratic Republic of the Congo and Angola. There, he will focus on security in the region, especially as it pertains to the Congo. He does not forget an obligatory stop by programs that are a part of the Presidents Emergency Plan for AIDS Relief.John Kerry at Gandhi Memorial Hospital, in Addis Ababa
But will Kerry remember to press Ethiopia on its press crackdowns when talking to them about democracy?
Last week, six members of the Zone Nine blogging collective were arrested. The bloggers have been critical of the government and its programs. Reports indicate that they are being held in a detention center in Ethiopia’s capital city, Addis Ababa.
The group stand accused of inciting public violence through social media and working foreign organizations. The actions were quickly decried by the Electronic Frontier Foundation, Human Rights Watch and the Committee to Protect Journalists. Kerry’s trip to Ethiopia is garnering attention from the rights groups.
“We hope that Secretary Kerry will recognize that peace and democracy are not compatible with censorship, intimidation, pervasive surveillance, and a crackdown on free expression and independent media,” wrote the Electronic Frontier Foundation.
The issue of press freedom is evidently on Sec Kerry’s radar. He responded to a tweet by New York Times journalist Nick Kristof regarding the recent arrests in Ethiopia

የትግል አቅጣጫውን ያላወቀ እና በማእበል ላይ ያለ ጀልባ አንድ ናቸው!!

May 2, 2014
ከዮሴፍ
ህወሃት ወያኔ በተደናገጠ ወይም በበረገገ ቁጥር አዲስ ነገር ይዞ ብቅ ማለቱ የተለመደ ነው። በተለይም ህዝብ ከህዝብ ከፋፍሎ እና አጋጭቶም ሆነ ከትውልድ ስፋራው እያፈናቀለና እየገደለም ቢሆን የስልጣነ መንበሩን መነቃነቅ ባሸተተ ቁጥር ሁሌም ዛሬም ነገም ከዚህ አደጋ የሚወጣበትን መንገድ መፈልፈሉ የሚታወቅ ሃቅ ነው። እንደ 40/60 ኮንዶሚኒየም አሁን በተለይም በቅርብ ጊዜ ካየናቸው የፖለቲካ ትግሉን አቅጣጫ ለማስለወጥ ሟቹ አምባገነኑ መለስ ዜናዊ በአንድ ጀምበር ከተኙበት ባነው “አባይን መገደብ አለብን ህዝቤ ሆይ ተከተለኝ፣ አባይን የደፈረ… ብላችሁም ዘምሩልኝ” በሚል የአረቡ አለም የነጻነት አቢዎት በግብጽ፣ ሊቢያ እና ቱኒዚያ የተጀመረው አምባገነኖችን ጠራርጎ የወሰደው የነጻነት ወራጅ ውሃ እንዳይወስደው ግድብ ሊያበጅለት ዘንድ የአባይን ሳይሆን የነጻነት ጩኸትን ሊገድብ ዘዴ ፈጠረ። በዚህም የዲያስፖራውንና የሀገሩን ውስጥ ህዜብን ይህ እኮ ሀገራዊ ጉዳይ ነው በፖለቲካ ብንለያይ በአባይ ላይ ግን አንድ ነን በሚል ብልጣብልጥ ዘዴ ንጹሃንን የሚያስርበት፣ የሚገድልበት ገንዘብ ነገር ግን በአባይ ስም ልመና ሞከረ አልተሳካም እንዴውም በውጪ ለስብሰባ አዳራሽና ለባለስልጣኑ ትራንስፖርትና ሌሎች ተጨምረው ያወጣቸው ብሮች ለስራው ቢውል የተሻለ ነበር በሚል የውስጥ ወቀሳም ደረሰበት። ታዲያ ለጊዜውም ቢሆን survive ለማድረግ በመምሰል ቢንገዳገድም የገባበት አላማ ለእውነተኛ ግድብ ባለመሆኑ ዛሬ አለም አቀፍ ባለሙያዎች “ጥናት ያልተደረገበት ነውና ይደረግ” በሚል ሙያዊ ልገሳቸውን ቢሰጡም ይህን ችላ ብሎ ለሀገር ተቆርቋሪ በመመስል በሁሉም ዘርፍ የተጀመረበትን የትግሉን አቅጣጫ ለማስቀየር አሁንም እየሞከረ ነው።
በአንጻሩ ለሱዳን በጎንደር መተማ የነጻነት ሃይሎች የእምቢተኝነት ድምጻቸውን፣ ጉልበታቸውን አጠናክረው እንዳይመጡበት እጅ መንሻ ይሆን ዘንድ እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር ስምምነት አደረግን በሚል May 21, 2008 መለስ ዜናዊ መሬት ለሱዳን መሰጠቱን እንዲህ ሲል ነገረን We, Ethiopia and Sudan, have signed an agreement not to displace any single individual from both sides to whom the demarcation benefits. We have given back this land, which was occupied in 1996. This land before 1996 belonged to Sudanese farmers. There is no single individual displaced at the boarder as it is being reported by some media. አቶ ስዪ አብርሃ በአንድ ወቅትም ይህ መሬት መሰጠቱን ለቪ.ኦ.ኤ ጋዜጠኛ እውነት መሆኑን አረጋግጠዋል። አሁን ደግሞ ሃይለማርያም ደሳለኝ ቀጠሉበት። መከረኛ አማራው በየሄደበት መሬቱን እየለቀቀ እንዲሰደድም አደረጉ። ታዲያ ይህ እንግዲህ በጣም ቀላሉ ማንም የሚያውቀውን እውነት ነው።
ስለዚህ ይሄን ዘረኛ ሀገራዊ ራእይ የሌለው ቡድን ሁሌ በየጊዜው በሚሰጠን አጀንዳ እየታለልን ለምን የትግል መስመራችንን እንስታለን? ፖለቲከኞች የሚታገሉለትን እና የሚታገሉበትን ዘዴ በትክክል ይዘው ካልሄዱ፣ ባለሙያዎችም ይህን ተረድተው ብእራቸውን አስተካክለው መታገል ያለባቸውን ካላወቁ አውቀነውም ሆነ ሳናውቀው ለወያኔ የትግል ዘዴ እየተመቻችን ነው። ለዚህ አባባሌ ምክንያት የሆነኝ ሰሞኑን እነ ዶ/ር ሚንጋ ነጋሽ፣ ፕሮፌሰር ማሞ እና ዶ/ር ስይድ ስለ አባይ የጻፉት Misplaced Opposition to the Grand Ethiopian Renaissance Dam” ጽሁፍ ነው። በእኔ እምነት 50+ የሆነው ኢትዮጵያዊ ግድቡን አይቃወምም ነገር ግን መቅደም የሚገባውና መገደብ ያለበት የወያኔ የጥይት አፈሙዞች የሚተፉትን እሳት ነው። በመሆኑም ተቃዋሚው ጎራ የአባይ አጅንዳ የመጣው ለማደናበር መሆኑን በደንብ በተረዳበት ሰአት፤ በታቃዋሚው ጎራ የሚታወቁት ግለሰቦች ወያኔ እንኳን ከልቡ መገደብ ሳይፈልግና ብሄራዊ ተቆርቋሪ መስሎ ለመቅረብ ያሰበውን አጀንዳ ተቀብሎ ማጨብጨብ የትግሉን አቅጣጫ ማስለወጥ ተገቢ አይደለም። ሰሞኑን እንኳን ሰላማዊ ሰልፈኞችን ወደ 30 የሚያህሉ ንጹሃንን የገደለ መንግስት እንዴት ሆኖ ነው ብሄራዊነት የሚሰማው? እናም ብእራችሁ ማእበል ላይ ሆኖ መወዛዎዝ የለበትም። እናንተ የጻፍችሁት ጽሁፈ-ጥናት የወያኔ መንግስት የውጪ አምባሳደሮች ወይም የኢትዮጵያ ኢምባሲ በአሜሪካ ዌብሳይት ወይም አይጋ ፎረም ላይ የሚለጠፍ ጽሁፍ ሆኖ ነው ያገኘሁት። ስለዚህ በኢትዮጵያ ህዝብ እና ሏኡላዊነት የሚደርሰውን በደል ማስቀደም ከተማሩ ፖለቲከኞች የሚጠበቅ ነው። መጻፋችሁ ጥሩ ነው ነገር ግን እኛ እናንተን የምናውቃችሁ ደግሞ በተቃዋሚነት ነውና በማእበሉ ተናውጣችሁ ካልተቀየራችሁ በስተቀር እናንተ የኢትዮጵያን ልጆች ሃብት ናችሁ እና እባካችሁ የትግሉን አቅጣጫ አትለውጡት። የወገኖቻችሁ፣ የሀገራችሁ ህዝብ በመሬት ስንጠቃ፣ በግድብ ሰበብ ከቀዪው እየተፈናቀለ ነው እና ያንን እናተኩር። የዶ/ር አክሎግ ቢራራ ኢትዮጵያዊነትን አጥፍቶ አባይን መታደግ ይቻላልን? የሚለው ሙያዊ ገለጻ በሚገባ አስቀምጦታል። እርግጥም እንዳሉት ኢትዮጵያዊነትን አጥፍቶ አባይን መታደግ ይቻላልን? ባሉት ጽሁፋቸው “አባይ ፈንጅ የቀበረ ውሃ ነው”። እኛ የጠማን ውሃ ነው! እኛ ያጣነው መብራት ነው! ስለዚህ አባይ የኛ ነው!! ነገም ዛሬም ትላንትም! የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ለወያኔ የስልጣን መቆያ እንጅ መንሻ እንዲሆን አንፈልግም። ኢትዮጵያኖች በወያኔ አጅንዳ ውስጥ ገብተን አንዋኝም። አጥቂዎች እንጂ ተከላካዮች አይደለንም። እናም ግድ የለም እናንተ የምትሉትን እነሱው ካወቁበት በዲፕሎማሲ ቋንቋ በተለመደ ውሸታቸው ይበሉት። እናንተ ግን የእኛ ናችሁ። ተሳሳትሁ እንዴ?

አንድነት ፓርቲ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ “የእሪታ ቀን” በሚል ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ይቀላቀሉ! (ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር)

May 2, 2014
ጤና ይስጥልኝ
ግዛቸው ሽፈራው እባላለሁ። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀመንበር ነኝ። አንድነት በኢትዮጵያ ሕጋዊ ፍቃድ አግኘቶ፣ በአገሪቷ ባሉ ክልሎች ሁሉ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀሰ ድርጅት ነው። አንድነት ከማንም ኢትዮጵያዊና ድርጅት ጋር ፀብ የለዉም። የአንድነት ፖለቲካ የኢትዮጵያዊነት፣ የፍቅርና የመቻቻል ፖለቲካ ነው። አላማችን ፣ የበለፀገች፣ ልጆቿ፣ በዘር ፣ በሃይማኖት፣ በጾታ ልዩነት ሳይደርገባቸው እኩል የሆኑባት፣ አንድነቷና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን መመስረት ነው።
አሁን በስልጣን ላይ ያለው የኢሕአዴግ መራሹ መንግስት፣ ግልጽነት የጎድለው፣ ተጠያቂነት የሌለው፣ በሙስና የተዘፈቀና የመልካም አስተዳደር ችግር ያለበት እንደመሆኑ፣ በሕዝብ ላይ ትልቅ በደል እያደረሰ ይገኛል። የሚከተለው የተሳሳተና ጎጂ የመሬት ፖሊሲ፣ ዜጎች፣ በልማት ስም፣ በቂ ካሳ ሳይከፈላቸው፣ ከቤታቸው እና ከእርሻ ቦታቸው በኃይል እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው። የሰብአዊ መብት ረገጣው፣ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ….. በግፍ መታሰራቸው፣ የኑሮ ዉድነቱ ሕዝቡ ከሚሸከመው በላይ እየሆነበት ነው።
ሕዝባችን ከዚህ የተሻለ ይገባዋል። ኢትዮጵያዉያን አሁን ያለውን አሳዛኝ ሁኔታ አንቀበለም በማለት፣ ለዉጥ መጠየቅ፣ ባለስልጣናትን ተጠያቂ ማድረግ ይኖርብናል።
ሕዝቡ ድምጹን ማሰማት የሚችልበት መድረክ ያገኝ ዘንድ፣ አንድነት፣ በሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እውቅና ያገኘበት፣ ሁለት ታላላቅ ሰላማዊ ሰልፎች ፣ እሑድ ሚያዚያ 26 ቀን፣ በአዲስ አበባ እና በደቡክ ክልል በምትገኝ የድራሼ/ጊዶሌ አዘጋጅቷል። የአዲስ አበባ እና የጊዶሌ ነዋሪዎች፣ በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን እንዲያሰሙ በአክብሮት ጥሪ አቀርባለሁ። ነጻነት ነጻ አይደለም። ነጻነትን ከሌሎች አናገኝም። ነጻነትን እኛዉ እራሳችን ነን ለራሳችን ማወጅ የምንችለው። እራሳችንን በግል ካያነው፣ ምንም ማድረግ የማንችል፣ አንድ ተራ ሰው አድርገን ልንቆጠር እንችላለን። ነገር ግን ተራ ሰዎች፣ በሚሊዮን ሲቆጠሩ፣ እነርሱን ማነቃነቅ የሚችል ምንም ኃይል አይኖርም። እንነሳ። ሰልፍ እንዉጣ። ድምጻችንን እናሰማ። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን ! እራሳችንን ነጻ በማወጣት አገራችንን ነጻ እናውጣ!
እንግዚአብሄር አገራችን ኢትይጵያን ይባርካት
ግዛቸው ሽፈራዉ
UDJ Addis Ababa demonstration on May 4

ሰበር ዜና- የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ፕሬዝደንት ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ተሰደደ

May 2, 2014
Journalist Betre Yakobከሳምንት በፊት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት በአፍሪካ ህብረት ጋባዥነት የኢትዮጵያን ችግርና አፈና በተለይ በሚዲያው ላይ ያለውን ጫና እና ጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰውን አፈና ለመግለጽ ወደ አንጎላ አቅንተው ነበር፡፡ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ለአፍካ ህብረትም የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረቡና ለሰብአዊ መብት ኮሚሽነሩም መልስ መስጠቱ ይታወቃል፡፡
ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ስብሰባው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ አገሩ ለመመለስ በሚዘጋጅበት ወቅት የዓለም አቀፍ የጋዜጠኛ ማህበራትን ጨምሮ ሌሎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ እሱን ለማሰር የተደረገው ዝግጅት በተጨባጭ ማስረጃ ስላቀረቡለት መሰደዱን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች በታሰሩበት ወቅት ፖሊስ የበትረ ያቆብን ቤት በመፈተሸ ያገኘውን ወረቀት ሁሉ እንደወሰደም ምንጮቻችን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አንጎላ በተደረገው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ኮሚሽነሩን በግል እንዳገኛቸውና ኮሚሽነሩም በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ በመግለጽ እንዲሚያገኙት ቃል ገብተውለት እንደነበር ተገልጿል፡፡ በተጨማም ከበርካታ የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና በሚዲያው ላይ ስለሚደረገው ጫና የተወያዩ ሲሆን አብዛኛዎቹ በተለያዩ መንገዶች እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተውለት እንደነበር ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በስብሰባው ወቅት ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጹ ጽሁፎች ለተሰብሰብሳቢዎቹ ተበትነዋል፡፡
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ መቋቋም ያስፈራቸው ሌሎች የጋዜጠኞች ማህበራት በትረ ያቆብን ለሂውማን ራይትስ ዎች፣ ለሲፒጄ፣ ለአርቲክል 19ና ሌሎች የጋዜጠኞች ማህበራት ይሰራል፣ ይሰልላል፣ የእነዚህ ድርጅቶች ተላላኪ ነው፣ ሪፖርት ይጽፋል በሚል በመግለጫቸውና ‹‹የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ›› በተባለው ፕሮግራም ይከሱት እንደነበር ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አገር ውስጥ በነበረበት ወቅት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻል፡፡

Kerry’s Africa Trip Should Emphasize Rights (HRW)

HRW) – US Secretary of State John Kerry should raise concerns about endemic human rights violations when he visits Ethiopia, the Democratic Republic of Congo, and Angola, Human Rights Watch said today. Kerry will visit the three countries from April 29 to May 5, 2014.SMNE Urges Secretary Kerry to speak out
According to the State Department, Kerry will travel to Africa to “encourage democratic development, promote respect for human rights, advance peace and security, engage with civil society…and promote trade, investment and development partnerships in Africa.”
“These three African countries are tremendously important for the United States, so Secretary of State Kerry should be careful not to marginalize their poor human rights records,” said Sarah Margon, acting Washington director at Human Rights Watch. “During his visit, Kerry should emphasize that rights, development, and security are inextricably tied.”
In Ethiopia, Kerry should call on officials to release unconditionally all activists and journalists who have been arbitrarily detained or convicted in unfair trials, including the six bloggers and three journalists arrested on April 25 and 26. Kerry should also press the Ethiopian government to amend or repeal two repressive laws on association and terrorism that have been used to oppress activists, independent organizations, and the media, and to bring politically motivated prosecutions.
In Congo, Kerry should call on the Congolese government and parliament to move forward with the establishment of independent, credible, and effective specialized mixed chambers to prosecute serious abuses domestically, and to consult with donors, civil society, and other stakeholders in order to make improvements to the current draft law.He should also press Congo’s leaders to take concrete steps to arrest and prosecute, in credible and impartial trials, leaders of armed groups – including the M23 rebel group – as well as army officials implicated in war crimes and crimes against humanity.
In Angola, Kerry should urge the government to respect the rights to freedom of assembly and speech and cease harassment, arbitrary arrests, and detention of protesters and journalists. The Angolan government should open credible investigations into serious abuses by the security forces, including the abduction, torture, and murder of two protest organizers, which came to light in a leaked internal government report.
“Kerry should not let this important opportunity to raise human rights concerns go wasted,” Margon said. “Strong language on rights will resonate throughout the African continent.”